(ደጀ ሰላም፤ መጋቢት 11/2004 ዓ.ም፤ ማርች 20/2012/ READ THIS ARTICLE IN PDF)፦
·
በየቦታው የተከማቸው የቃጠሎ ፍሕም በጣም ብዙ ነው፤ በተደጋጋሚ ቃጠሎ የመቀስቀስ ዕድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ አሁን ባለን መረጃ ትናንት ሌሊት እና ዛሬ ጠዋት ዳግመኛ የተቀሰቀሰው እሳቱ በገዳሙ ከብቶች ማደሪያ በኩል ወደ ገዳሙ እያቀና ነው ተብሏል፡፡ ከጸሎቱ ባሻገር ለእሳቱ መጥፋት ዘላቂ መፍትሔ ለመስጠት እርጥበት አጠር ከሆነው አየር አኳያ ርግጠኛ ለመሆን ጉልበት ያለው የሰው ኃይል በጣም አስፈልጓል፡፡
· የዝቋላን ገዳም ቃጠሎ ለመከላከል የተሰማሩ ወጣቶች በጠቅላይ ቤተ ክህነት ናቸው - ተቃውሟቸውን ለመግለጽ፣ ጥያቄያቸውንም ለማቅረብ፡፡ ፖሊስ ወጣቶቹ እንዲበተኑ እያዘዘ ነው፡፡
· ከፍተኛ
ቁጥር ያለው ምእመን ቃጠሎውን ለመከላከል የሚረዱ የግል መሣሪያዎችን (ጄሪካን፣ የቁፋሮ፣ መቁረጫ መሣሪያዎች) እና ደረቅ ስንቅ
በመያዝ ከአዲስ አበባ፣ አዳማ እና ቢሾፍቱ ወደ ዝቋላ እየተመመ ነው፡፡
ቸር ወሬ ያሰማን
አሜን
Picture: Courtesy of Nigusie Girma
የዝቋላን ገዳም ቃጠሎ ለመከላከል
እየተደረገ ባለው ጥረት፡-
· ቃጠሎውን
ጨርሶ ለማጥፋት የአቢሲኒያ የበረራ አገልግሎት አውሮፕላን ለመስጠት ፈቃደኛ ነው፤ ሂሊኮፕተርም ከአየር ኀይል ለማግኘት ዕድሉ አለ፤
ይሁንና የመርጫ መሣሪያ ቴክኖሎጂ በአገሪቱ የለም፤ የኬሚካሉም መወደድ ችግር ሆኗል፡፡
· አሁን ባለው
የቴክኖሎጂ አቅም በዝቅተኛ ከፍታ እየበረሩ ወደ ጥልቁ ገደልና ጫካ ውኃ ብቻ ለመርጨት ቢሞከር አደጋ መጋበዝ ይሆናል፤ በከፍታ በረራ
ቢረጭ ደግሞ ውኃው አየር ላይ ነው የሚቀረው፡፡ በመሆኑም ዘልቆ ሊወርድ የሚችለውን የማጥፊያ ኬሚካል በውድ ዋጋ ለማግኘት ቢቻል
እንኳ የመርጫ መሣሪያው በእጅጉ አስፈላጊ ይሆናል፡፡
· የአደጋ
መከላከልና ዝግጁነት ያሰማራው ኀይለ ግብር የተዳፈነው እሳት አሁን ካለበት የባሰ እንዳይዛመት እሳተ ከላ(Fire Break)
በግንድ፣ በቅጠሉ መሥራት እንደ ተሻለ አማራጭ ውስዶ እየተረባረበ ነው፡፡ ቃጠሎውን ለመከላከል የሚመጡ ምእመናንም የዝቋላን አቀበት
ተቋቁመው ወጥተው በምንጣሮ፣ በቁፋሮ፣ በሸክም ለመራዳት የሚችሉ መሆን ይገባቸዋል፡፡
![]() |
| Picture: Courtesy of Nigusie Girma |
· የዝቋላን ገዳም ቃጠሎ ለመከላከል የተሰማሩ ወጣቶች በጠቅላይ ቤተ ክህነት ናቸው - ተቃውሟቸውን ለመግለጽ፣ ጥያቄያቸውንም ለማቅረብ፡፡ ፖሊስ ወጣቶቹ እንዲበተኑ እያዘዘ ነው፡፡
·
በጠቅላይ
ቤተ ክህነቱ ወጣቶቹን የሚያነጋግር ሓላፊ የለም፤ ዋና ሥራ አስኪያጁ ብፁዕ አቡነ ፊልጶስ ከፓትርያሪክ አቡነ ጳውሎስ ጋራ በአሁኑ
ሰዓት በቅዱስ ማርቆስ ካቴድራል እየተከናወነ በሚገኘው የብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሲኖዳ የቀብር ሥነ ሥርዐት ላይ ለመገኘት ትላንት ማምሻውን
ሄደዋል፡፡ ለጉዞው ከ44,000 ብር በላይ ወጪ ተደርጓል፡፡ ብሔራዊ የኀዘን ቀን የታወጀ ሲሆን ከሥነ ሥርዐቱ ፍጻሜ በኋላ የቅዱስነታቸው
አስከሬን በወታደራዊ ሄሊኮፕተር ተወስዶ ከካይሮ 100 ኪ.ሜ ርቀት ናይል ዴልታ ዋዲ ኤል ናጥሩን የቅዱስ ቢሾይ ገዳም እንደሚያርፍ ተዘግቧል፡፡
·
የገዳማት
አስተዳደር መምሪያ ሓላፊ ንቡረ እድ አባ ገብረ ማርያም ያሉበት ኮሚቴ ቃጠሎው ከተነሣ አራት ቀናት በኋላ ዛሬ ወደ ዝቋላ አምርቷል፡፡
የምሥራቅ ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ ጎርጎርዮስ በገዳሙ ጸሎተ ቅዳሴ ላይ ናቸው፡፡
![]() |
| Picture: Courtesy of Laekemariam Dibabu |
·
በተለያዩ
የብዙኀን መገናኛዎች እሳቱ ጨርሶ እንደጠፋና ለመከላከል እንደተቻለ የሚሰራጨው ዘገባ በቦታው በመሬት ላይ ከሚታየው ሐቅ ጋራ ያልተጣጣመ
በመሆኑ ሳንዘናጋና ሳንሳነፍ ታሪካዊ ግዴታንን ባለን አቅም እንወጣ!!!



6 comments:
UUUUU....UUUUU.....UUUU.....ABUYE DIRESULIN. ABUYE YIKIR BELUN, ABUYE MARUN, ABUYE IRDUN, ABUE IZENULIN, ABUYE MARUN, ABUYE ATKEYEMUN, ABUYE NULIN, ABUYE ISATUN MELSULIN, ABUYE IRDUN. UUUUUUUUU.....
wegen yihe hulu yegnaw hateyat new ebakachehu atebken entseleyy gedamatem eyeheden bealem yelemdenewen metefo megebar enetew ahun ahun yemitayew setuna wendu cherash gedam mehonun zengetoal aboyee yetkotu yemselal selezhi yihen sew ayedelem yametaw yeamelak kuta new enmeles wegennn egziooooo
የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ጠላት እንጅ የኢትዮጵያን ህዝብ የሚወክል መንግስት የለንም:: መንግስት ቢሆን ኖሮ ለህዝብ ይቆማል እንጅ በህዝብ ላይ አያላግጥም ነበር :: ሁሉንም በተረጋጋ መንፈስ እንዳመጣጡ ማስተናገድ ነው :: እስከመጨረሻው የፀና እርሱ ይድናል :: ጎልያድን ባንዲት ጠጠር ያስወገደ እንዚህን የዘመናችን ጎለያዶችን መለስንና አባ ጨጔሬን ከፊታችን ያስወግድልን:: በቀረውስ ሁሉም ለኛ ለ ለተጋድሎና ለበረከት ስለሆነ ሁሉንም በአኮቴት እንቀበለዋለን::
OOO Jesus Christ Son of God, have Mercy on us, sinners!
ወንድሜና እህቴ ሆይ፦
“የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ጠላት እንጅ የኢትዮጵያን ህዝብ የሚወክል መንግስት የለንም::” ላልከው(ሽው) ጉዳይ ለመጨመር ያክል ይህን ብል ይፈቀድልኝ? መንግስት እኮ ሕዝብ ነው፤ ሕዝብ ያልደገፈው መንግስት በየትኛውም የአለም ክፍል አይኖርም፤ አዎ ምናለባት አፈሙዝ በመጠቀም የደፋሮችን አፍ የሚያስይዙ ይኖራሉ ግን ሁሉም ሕዝቦች እስከሚደፍሩ ነው። ምሳሌ፦ ግብጽ፣ ሊቢያ፣ ይምን፣ ራሽያ፣ ወዘተ …….
አገራችን ዛሬ ያጣችው እውነተኛ ሃዋርያዊ የእምነት አባት ነው። መንፍስ ቅዱስ እንጂ ሕዝብ ሊዳኘው የማይችል መሆኑን ከእለት እለት መጠጊያ አድርጎ የተቀመጠው ሴኖዶስና እነዲመራው የመረጣቸው ፓትርያርክ ናቸው ለዚህ ሁሊ ቃጠሎ ተጠያቂዎች።
በሙሴ ጊዜ እንደቀለጠው የወርቅ ጥጃ ምስል፡ የፓትርያርኩን ምስል ማቅለጥ አቅቶአቸው ቤተ ክርስቲያን ስትቀልጥ እነርሱ እየሞቁ ነው የሚታዩት። መንግስት ምን ያድርግ፤ የቤቱ ባለቤት የሆኑት ጳጳሳቱ መቸ ጮሁና፤ ምእመናኑ ቢጮህም መንግስት ሊሰማ የሚችለው ከፓትርያርኩ ሲጠየቅ ነውእኮ።
ቅጣቱ ከእግዚአብሔር ነውና አባቶቻችን በጣሊያን ጊዜ እንዳደረጉት ጽላት ይዘን እግዚኦ መሃረነ እንበል። ሱባየ በአለም ላይ ባለችው አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ ይታወጅ፤ መለከት ይነፋ፣ እንጹም፣ እንስገድ። የእውነተኛ አባቶች ካሉን ይህንን ያድርጉልን። አለበለዚያ ግን ቂም ይዞ አሃዱ ማለትና ሳይፈቱ ይፍታህ(ሽ) ማለቱ የባሰ ማእበልና ቸነፈር ነው በአገሪቱ ላይ የሚነፋባት።
እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ እንበል (41)
ወንድሜና እህቴ ሆይ፦
“የኢትዮጵያና የኢትዮጵያውያን ጠላት እንጅ የኢትዮጵያን ህዝብ የሚወክል መንግስት የለንም::” ላልከው(ሽው) ጉዳይ ለመጨመር ያክል ይህን ብል ይፈቀድልኝ? መንግስት እኮ ሕዝብ ነው፤ ሕዝብ ያልደገፈው መንግስት በየትኛውም የአለም ክፍል አይኖርም፤ አዎ ምናለባት አፈሙዝ በመጠቀም የደፋሮችን አፍ የሚያስይዙ ይኖራሉ ግን ሁሉም ሕዝቦች እስከሚደፍሩ ነው። ምሳሌ፦ ግብጽ፣ ሊቢያ፣ ይምን፣ ራሽያ፣ ወዘተ …….
አገራችን ዛሬ ያጣችው እውነተኛ ሃዋርያዊ የእምነት አባት ነው። መንፍስ ቅዱስ እንጂ ሕዝብ ሊዳኘው የማይችል መሆኑን ከእለት እለት መጠጊያ አድርጎ የተቀመጠው ሴኖዶስና እነዲመራው የመረጣቸው ፓትርያርክ ናቸው ለዚህ ሁሊ ቃጠሎ ተጠያቂዎች።
በሙሴ ጊዜ እንደቀለጠው የወርቅ ጥጃ ምስል፡ የፓትርያርኩን ምስል ማቅለጥ አቅቶአቸው ቤተ ክርስቲያን ስትቀልጥ እነርሱ እየሞቁ ነው የሚታዩት። መንግስት ምን ያድርግ፤ የቤቱ ባለቤት የሆኑት ጳጳሳቱ መቸ ጮሁና፤ ምእመናኑ ቢጮህም መንግስት ሊሰማ የሚችለው ከፓትርያርኩ ሲጠየቅ ነውእኮ።
ቅጣቱ ከእግዚአብሔር ነውና አባቶቻችን በጣሊያን ጊዜ እንዳደረጉት ጽላት ይዘን እግዚኦ መሃረነ እንበል። ሱባየ በአለም ላይ ባለችው አጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ሁሉ ይታወጅ፤ መለከት ይነፋ፣ እንጹም፣ እንስገድ። የእውነተኛ አባቶች ካሉን ይህንን ያድርጉልን። አለበለዚያ ግን ቂም ይዞ አሃዱ ማለትና ሳይፈቱ ይፍታህ(ሽ) ማለቱ የባሰ ማእበልና ቸነፈር ነው በአገሪቱ ላይ የሚነፋባት።
እግዚኦ መሃረነ ክርስቶስ እንበል (41)
Post a Comment