(ማኅበረ ቅዱሳን):- በምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ወንበርማ ወረዳ የሚገኙ ከ400 በላይ የሚሆኑ የጉምዝ ብሔረሰብ አባላት በጎመር ቅድስት ክርስቶስ ሰምራ ቤተ ክርስቲያን እሑድ የካቲት 13 ቀን 2003 ዓ.ም በብፁዕ አቡነ በርናባስ የምዕራብ ጎጃም ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ በሀገረ ስብከቱ ቆሞሳትና ካህናት መጠመቃቸውን የማኅበረ ቅዱሳን የባህር ዳር ማዕከል ገለጸ፡፡
February 27, 2011
February 25, 2011
በዐውደ ምሕረት ላይ ስሙን በማጥፋት በተሰማሩት ጥቅመኞች እና ይህን ተግባር በሚያበረታቱ አካላት ላይ ቅ/ሲኖዶስ ርምጃ እንዲወስድ ማኅበረ ቅዱሳን ጠየቀ
ማውጫ፦
ሐተታ
Posted by
DejeS ZeTewahedo
- ማኅበሩ በቋሚ ሲኖዶሱ ውሳኔ ማዘኑን ገልጧል::
- “የሐዋሳ ከተማ ምእመናን ጥያቄ የሃይማኖታዊ መብት ጥያቄ እንጂ የማንም አለመሆኑን ተረድተናል፡፡”
(ደጀ ሰላም፤ ፌብሩዋሪ 25/2011፤ የካቲት 18/2003 ዓ.ም):- በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን በሲዳማ ጌዲኦ፣ አማሮ እና ቡርጂ ዞኖች እና ልዩ ወረዳዎች ሀገረ ስብከት በሐዋሳ ከተማ ከ2002 ዓ.ም ወዲህ ከተከሠተው የቤተ ክርስቲያን አስተዳደር ችግር ጋራ በተያያዘ እየተደረገበት ያለው የስም ማጥፋት ዘመቻ እንዲቆምለት ጠየቀ፡፡
February 19, 2011
የሐዋሳ ጉዳይ አጠቃላይ ሪፖርታዥ
ማውጫ፦
ሐተታ
Posted by
DejeS ZeTewahedo
- የደቡብ ክልል ርእሰ መስተዳድር ከሐዋሳ ቅዱስ ገብርኤል ገዳም ምእመናን ጋራ ተወያዩ
- ርእሰ መስተዳድሩ የገዳሙን አገልግሎት እና ጸጥታ የሚያውኩ “ድንጋይ ወርዋሪዎችን” አስጠንቅቀዋል
- “ከአሁን በኋላ የማዳምጠው የሀገረ ስብከቱን ሊቀ ጳጳስ አቡነ ገብርኤልን ብቻ ነው፤ እሰር ካሉኝ አስራለሁ፤ ማናችሁም ከእርሳቸው ውሳኔ ውጭ መሆን አትችሉም፡፡”(አቶ ሺፈራው ሽጉጤ)
- “ቤተ ክርስቲያን የአንድ ክልል አይደለችም፤ ዘረኝነትን ትቃወማለች፤ በዘረኝነት ልትታወክ አይገባም፡፡”(ብፁዕ አቡነ ገብርኤል)
- የርእሰ መስተዳድሩ አቀራርቦ የማወያየት ጥረት ፓትርያርኩን እና ጠቅላይ ቤተ ክህነቱን ክፉኛ አስነቅፏቸዋል
(ደጀ ሰላም፤ ፌብሩዋሪ 19/2011፤ የካቲት 12/2003 ዓ.ም):- ተቃውሟቸውን በሰላማዊ መንገድ ከማቅረብ ይልቅ “ጠጠር መወርወር” በሚመርጡ ሁከተኞች ላይ አስተዳደራቸው ርምጃ እንደሚወስድ የደቡብ ብሔር ብሔረሰቦች እና ሕዝቦች ክልል ፕሬዝዳንት አቶ ሽፈራው ሽጉጤ አስጠነቀቁ፡፡ “ፍላጎታችን ተስማምታችሁ አምልኮታችሁን እንድትፈጽሙ ነው፤ ማንኛውንም ተቃውሞ ተዋረዱን ጠብቆ በሰላማዊ መንገድ ማቅረብ ይቻላል፤ የአድማ ስብሰባ አይፈቀድም፤ ጠጠር እወረውራለሁ የሚል ካለ ጠባችን ከእርሱ ጋራ ነው፤ ለእርሱ የተዘጋጀ ስፍራ አለ - አቦስቶ! እዚያ ወስደን እናሳርፈዋለን!!” ያሉት ፕሬዝዳንቱ፣ ሀገረ ስብከቱን በተመለከተ በመስተዳድሩ ዘንድ ተቀባይነት የሚኖረው እና ተፈጻሚነት የሚያገኘው የሊቀ ጳጳሱ ብፁዕ አቡነ ገብርኤል ውሳኔ ብቻ በመሆኑ ማናቸውም ወገኖች ከብፁዕነታቸው ውሳኔ ውጭ መንቀሳቀስ እንደማይችሉ ለተሰብሳቢዎቹ በአጽንዖት ተናግረዋል፡፡
February 10, 2011
የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ አፅራረ ቤተ ክርስቲያንን ለመከላከል በሚያደረገው ጥረት ማንኛውንም ድጋፍ እንደሚሰጥ የአ/አበባ ሀ/ስብከት አስታወቀ
ማውጫ፦
ዜና
Posted by
DejeS ZeTewahedo
- የፕሮቴስታንታዊ-ተሐድሶ-ኑፋቄ ጥመት - አሰግድ ሣህሉ እንደ ማሳያ (ከደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተ ክርስቲያን ሰንበት ት/ቤት ዘገባ የተገኘ)
![]() |
| ቀንደኛ የተሐድሶ ኑፋቄ አቀንቃኝ የተባለው አሰግድ ሣህለ |
(ደጀ ሰላም፤ ፌብሩዋሪ 10/2011፤ የካቲት 3/2003 ዓ.ም)፦ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን ሐዋርያዊ ተልእኮ ለማፋጠን እና ለማስፋፋት፣ የተቋቋመበትን ዓላማ ለማሳካት፣ ኮሌጁንም ከማንኛውም አጽራረ ቤተ ክርስቲያን አካላት ለመጠበቅ በሚያደርገው ጥረት ሁሉ ድጋፍ የሚሰጥ መሆኑን አስታወቀ፡፡ የሀገረ ስብከቱ ጽ/ቤት ይህን ያስታወቀው፣ የኮሌጁ አስተዳደር ጉባኤ የኮሌጁን የቅበላ መስፈርት ባለማሟላቱ ኅዳር 23 ቀን 2003 ዓ.ም ከትምህርት ገበታ ያገደው አሰግድ ሣህለ የተባለ ቀንደኛ የተሐድሶ ኑፋቄ አቀንቃኝ፣ ‹‹በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ውስጥ የቤተ ክርስቲያን አባል እንደሆነ የሚያቀርበው የመብት ጥያቄ ተቀባይነት የሌለውና በሀገረ ስብከታችን ውስጥ የቤተ ክርስቲያናችን አባል አለመሆኑን›› በመግለጽ ለኮሌጁ በጻፈው ደብዳቤ ነው፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)



