
(ደጀ ሰላም፤ ፌብሩዋሪ 27/2010)፦ የ“አርማጌዶን” ነገር ከተነሣ ወዲህ በኢትዮጵያ በሰባክያን፣ በዘማርያንና ጊዜ-ፈጠር (ዘመነኞች) የሆኑ አገልጋዮችን የተመለከተው ውይይት ቀጥሏል። ከኢትዮጵያ ውጪም “ደጀ ሰላም” በከፈተቻቸው መድረኮቿ አማካይነት ውይይቱ ቀጥሏል። የነገሩ ባለቤቶች የሆኑት ሰዎችም በየመጽሔቱ የየራሳቸውን ማለት ጀምረዋል። አስቀድሞ ዲ/ን በጋሻው፣ አሁን ደግሞ መምህር ዘመድኩን የየራሳቸውን ብለዋል። እናንተ ደጀ ሰላማውያን ሁለቱንም ተመልክታችሁ አስተያየታችሁን ትሰጣላችሁ። ደጀ ሰላም የሁለቱንም ወገን ታስተናግዳለች። ለቤተ ክርስቲያናችን የሚበጀውን እንድንወስድ፣ ስንዴውን ከእንክርዳዱ እንድንለይ ትመክራለች።
እነሆ!!!

















