(ማ/ቅዱሳን ድረ ገጽ):- በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከመስከረም 26 ቀን እስከ ኅዳር 6 ቀን ያለው ጊዜ ወርኀ ጽጌ ይባላል፡፡ ይህ ወቅት ምድር በአበቦች ቀለምና መዓዛ የምታጌጥበት በመሆኑ «የአበባ ወር» ወርኀ ጽጌ ተብሏል፡፡
አበባ የፍሬ እናት ነው፡፡ አበባን ያየ ሰው ሕይወቱ በተስፋ ትሞላለች፡፡ መልካሙ ፍሬ ከአበባው ይገኛልና፡፡ እመቤታችንም የተባረከ ፍሬ መድኃኒተ ዓለም ኢየሱስ ክርሰቶስን ያስገኘች አማናዊቷ አበባ ናት፡፡ የአዳም ተስፋ መፈጸሙን፣ የነቢያት ትንቢት መድረሱን ያበሰረችን የድኅነት ምልክት እርሷ ናት፡፡ «ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል» እንዳለ ነቢየ ልዑል ኢሳይያስ (ኢሳ 7÷14)፡፡
የአበቦች መፍካት የጥጋብ ዘመን መምጣጡን ያበስራል፡፡ ወርኃ ክረምት ዘር ገና በምድር ላይ ስለሆነ ጎተራው ይሟጠጣል፡፡ መሶቡ ድንግጥ ይላል፡፡ የክረምቱ ጊዜ በጎመንና በቅጠላ ቅጠሉ በጥራጥሬው ጭምር ይወጣል፡፡ ከአዲሱ ዘመን መባቻ ጀምሮ ግን «የጎመን ምንቸት ውጣ የገንፎ ምንቸት ግባ» በሚለው ባሕላዊ አገላለጽ የአዲስ እህል ሽታ ይሰማል፡፡ የእሸት ጊዜ ይታያል፡፡ ይህ ጊዜ ምድር በሥነ ጽጌያት ( በአበቦች ኅብር) አጊጣ፣ ሰማይ በከዋክብት አሽብርቆ የሚታይበት፣ የጠራ ውኃ ከወንዞችና ጅረቶች የሚፈስበት፣ ንፁሕ አየር የሚነፍስበት፣ አዕዋፍ ከተሰደዱበት እየተመለሱ የሚዘምሩበት፣ እንስሳትና አራዊት ለምለሙን ሳር እየነጩ ጥሩውን ወሃ እየተጎነጩ የሚፈነድቁበት ጊዜ ስለሆነ ለፍጥረት ደስ ይላል (መኃልይ 2÷13)፡፡
«የዘንድሮን ክረምት ወጣናት በመላ
አንድ ቀን ሰናድር አንድ ቀን ስንበላ
እኛስ ይችን ክረምት ወጣናት በመላ
በኩርማን እንጀራ ጎመን ተጠቅልላ»
እንደሚባለው ክረምት ያለችውን አብቃቅቶ የሚከረምበት ጊዜ ነው፡፡ አበቦች በጋራ በሽንተሩ ሲፈነዱ ማሳውና ጓሮው ሲያብብ ግን የጥጋቡ የእህሉ ወቅት መምጣቱን ይናገራሉ፡፡
የድኅነት ምግብ የጽድቅ ውኃ አጥቶ በሲዖል በረሃ በጽድቅ ረሃብ ለተንገላታው የአዳም ዘር ነፍስ በእግዚአብሔር ቸርነት በጌታችን ሥጋና ደም በጸጋ መንፈስ ቅዱስ የምትጠግብበት ዘመን መድረሱን ያበሠረችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት፡፡ ዛሬም ቢሆን የተስፋ መቁረጥና የጭንቀት፣ የደዌ ሥጋና የደዌ ነፍስ ረሃብ ለወደቀባቸው እመቤታችን የመዳን ተስፋቸው ናት፡፡ በዚህም የተነሳ ቅዱሳን አበው እመቤታችንን በአበባ መስለው ምስጢር ከምሳሌ በማስተባበር ስደቷን በወርኃ ጽጌ ያስቡታል፡
ይህ የእመቤታችን መታሰቢያ ወር በቤተክርስቲያናችን የሚከበረው በሚከተለው ሁኔታ ነው፡፡
1ኛ. በማኅሌት
2ኛ. በቅዳሴ
3ኛ. በዝክር
ማኅሌት
ነቢየ እግዚአብሔር ዳዊት፣ በአምላካችን ቤት በአደባባዮች የምትቆሙ እናንተ የእግዚአብሔር ባርያዎች ሁላችሁ በሌሊት እጃችሁን አንሱ፣ እግዚአብሔርንም ባርኩ (መዝ 133÷1-2) በማለት እንደተናገረው አባቶቻችን ከቅዳሜ ማታ እስከ እሑድ ጠዋት እንዲሁም በክብረ በዓላት እጆቻቸውን ለጭብጨባና ለሽብሸባ አንስተው፣ በከበሮና በጸናጽል እየወረቡ፣ በመቋሚያ እየዘመሙ፣ ያለ ድካምና መሰልቸት ሲዘምሩ ያድራሉ፡፡ ምዕመናንም እንቅልፍ ሳያታልላቸው፣ ድካም ሳይበግራቸው ከአባቶቻቸው ጋር በቤተክርስቲያን በመገኘት በዕልልታ በዝማሬ እያጀቡ ያድራሉ፡፡ በዚህ ወቅት የሚቀርበው ዝማሬ ሦስት ወገን ነው፡፡
1. ከቅዱስ ያሬድ ድጓ
ቤተክርስቲያናችንን በዓለም አቀፍ ደረጃ ካሳወቋት ሊቃውንተ ቤተክርሰቲያን መካከል አንዱና ዋነኛው ቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ የቅዱስ ያሬድ ዜማ ከአርያም የተገኘ በመሆኑ ጊዜ የማይሽረው ዘመን የማይለውጠው የቅድስት ቤተክርስቲያን አንጡራ ሀብት ነው፡፡
ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ዓመቱን ክረምት፣ መጸው፣ ሐጋይ ፀደይ ብሎ በመከፋፈል በየዘመኑ የሚዘመረውን መዝሙር አዘጋጅቷል፡፡ በወርኃ ጽጌም ቅዱስ ያሬድ የምድሪቱን በአበባ መሸለም፣ በቡቃያ ማማር፣ የክረምቱን የጭቃና የድጥ ወቅት ማለፍ በተመለከተ እግዚአብሔርን ካመሰገነበት ድርሰቱ እየተውጣጣ ይዘመራል፡፡ በተለይ በወርኀ ጽጌ፡፡
2. ማኅሌተ ጽጌ
ይህ መዝሙር የእመቤታችንን ታሪክ ከጽንሰቷ እስከ ልደቷ፣ ክብሯን፣ ንጽህናዋን፣ በሄሮድስ ምክንያት የደረሰባትን ስደትና መከራ የበረሀውን ጉዞ እያነሳ የሚያመሰግን ታሪካዊ ይዘት ያለው ድርሰት ነው፡፡
ማኅሌተ ጽጌን የደረሱት አባ ጽጌ ብርሃን የተባሉ ሊቅ መሆናቸው ይነገረል፡፡ ዘመኑም በ14ኛው ክፍለ ዘመን ነው፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስ የምሁርን ሕዝብ አስተምረው ወደ ይፋት በማምራት ወንጌልን በመስበክ ላይ እያሉ «ክርስቶስ ተወለደ፣ ሞተ፣ ተነሣ እያሉ እንዴት ያስተምራሉ;» በማለት አንድ አይሁዳዊ ሊቅ ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም በትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 11 ቁጥር አንድ ላያ የጻፈውን የነቢዩን ቃል («ከእሴይ ግንድ በትር ይወጣል፣ ከሥሩም ቄጥቋጦ ያፈራል» የሚለውን) ጠቅሰው ስላብራሩለት በትምህርታቸው አምኖ ተጠምቆ ለመመንኮስ በቅቷል፡፡ ስሙንም ጽጌ ብርሃን በማለት ሰይመውታል፡፡
አባ ጽጌ ብርሃን ምሁረ ኦሪት ስለነበረ አብሯቸው እየተዘዋወረ ሀዲስን ከብሉይ አስማምቶ ከተማረ በኋላ እንደ መዝሙረ ዳዊት 150 አድርጎ ማኅሌተ ጽጌን ከአማካሪው ከወረ ኢለኀው ተወላጅ ከአባ ገብረማርያም ዘደብረ ሐንታ ጋር በመሆን አዘጋጀው፡፡ ድርሰቱም ቤት እየመታ በአምስት በአምስት ስንኝ እየተከፈለ ነው፡፡
በዚህ ጊዜም ጾም የጌታንና የእመቤታችንን ስደትና መንገላታት በማሰብ ስለ ፍቅራቸው ባሕታውያን፣ መነኮሳትና አንዳንድ ምዕመናን በፈቃዳቸው ይጾማሉ፡፡
3. ሰቆቃወ ድንግል
«ሰቆቃ» ማለት ለቅሶ ዋይታ ማለት ነው፡፡ እመቤታች «ልጄን ይገድሉብኛል ብላ የሄሮድስ ወታደሮች ሲከተሏት፣ የዮሴፍ ልጅ ዮሳዕ የቤተልሔምን ሕጻናት እልቂት ሲነግራት፣ ጥጦስና ዳክርስ የተባሉ ከግብጽ ወደ እስራኤል በሚወስደው መንገድ በጋዛ በር የሚዘርፉ ሽፍቶች ሲያጋጥሟት ያለቀሰችውንና በተወደደ ልጇ ላይ የወረደውን መሪር እንባ በማስታወስ የሚዘመር ነው፡፡ ይህም መዝሙር በ15ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በደብረ ወርቅ ቤተክርስቲያን የድጓ መምህር በነበሩት በመምህር አርከ ሥሉስ እንደተደረሰ ይነገራል፡፡
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
http://mahiberekidusan.org/Default.aspx?tabid=88&ctl=Details&mid=371&ItemID=57
October 7, 2010
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
Blog Archive
-
▼
2010
(305)
-
▼
October
(63)
- “ሰውየውን” ታዲያ ማን እንበላቸው?
- ይድረስ ለቅዱስነትዎ
- ርእሰ አንቀጽ፦ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ “በቃ” ሊባሉ ይገባል፤
- አቡነ ጳውሎስ አልፈርምም ብለዋል፤ የሚከተለው ነገር ምንድን ነው?
- ፓትርያርኩ ቅዱስ ሲኖዶስ በጋራ ካዘጋጀው የተለየ ጋዜጣዊ መግለጫ በመስጠታቸው ሳ...
- ቅ/ፓትርያርኩ የቅ/ሲኖዶስን ውሳኔ የቀነጨበ መግለጫ አነበቡ
- ሰበር ዜና:- አቡነ ጳውሎስ በቃለ ጉባዔው ላይ አልፈርምም አሉ
- የምስጋና መልእክት ለብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት
- የቅ/ሲኖዱስ ምልአተ ጉባኤ ጠንካራ ውይይት በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ዙሪያ
- የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊነትና ሊገጥሙት የሚችሉት ፈተናዎች
- ቅ/ሲኖዶስ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የአ/አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሆኑ የደ...
- ምእመኑ ምን ይላል? (ክፍል 3)
- የአቡነ ጳውሎስ "ሐውልተ ስምዕ" በ20 ቀናት ውስጥ እንዲፈርስ ትእዛዝ ተሰጥቷል...
- ሰበር ዜና፦ ብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ የአዲስ አበባ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ ሆኑ
- ቅዱስ ሲኖዶስ በጳጳሳት ምደባ እና ዝውውር ጉዳይ በፓትርያርኩ በቀረበው ሐሳብ ...
- ይድረስ ለቅዱስ ሲኖዶስ አባላት፤ ስለ ብፁዕ አቡነ አብርሃም 2 መግለጫዎች
- ርእሰ አንቀጽ፦ የሀ/ስብከት ምደባ አጀንዳ አባቶች የምትለያዩበት/ የምትከፋፈሉበ...
- በጳጳሳት ዝውውር እና ምደባ ጉዳይ በፓትርያርኩ የቀረበው የውሳኔ ሐሳብ ከፍተኛ ...
- ምእመኑ ምን ይላል? (ክፍል 2)
- ቅ/ሲኖዶስ በሕንጻዎች እና ቤቶች አስተዳደር እና በልማት ኮሚሽን ውስጥ የሚፈጸሙ...
- ምእመኑ ምን ይላል? (ክፍል 1)
- የድምጽ አስተያየት
- “ሐውልቱ” ምን ይሁን?
- አባቶቻችን፤ እናመሰግናለን። ውሳኔው ይተገበር ዘንድ እንጠብቃለን
- የቅ/ሲኖዶስ የዛሬ ውሎ ዝርዝር ሪፖርታዥ
- ሰበር ዜና፦ ቅዱስ ሲኖዶስ የአቡነ ጳውሎስ ‹‹ሐውልተ ስምዕ›› እንዲፈርስ ወሰነ...
- የቅ/ሲኖዶስ የዛሬ ከሰዓት ውሎ፦ ቅዱስ ሲኖዶስ በሐውልቱ፣ በፖስተሩ እና በጠቅላ...
- ቅ/ሲኖዶስ 3ኛ ቀን ከሰዓት በፊት፦ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬን ከሥራ አስኪያ...
- የሐዋሳ ምእመናን የደረሰውን በደል በማስረጃ አቀረቡ፤ አጣሪው ተልዕኮውን ፈጽሞ ...
- የቅ/ሲኖዶስ አጀንዳዎች
- ሰበር ዜና፦ አባ ሰረቀ ብርሃን ደጀ ሰላምን እና ማ/ቅዱሳንን ሊከሱ ነው
- አጣሪ ኮሚቴው በሐዋሳ
- የቅ/ሲኖዶስ ሁለተኛ ቀን ውሎ
- አጣሪ ኮሚቴው ወደ ሐዋሳ ተጉዟል
- የቅዱስ ሲኖዶስ የዛሬ ውሎ
- ቅዱስ ሲኖዶስ ስለምን ጉዳይ ይነጋገራል?
- የሀገር ሽማግሌዎች አባቶችን ለማስማማት ሲሞክሩ ቆይተዋል
- የቅ/ሲኖዶስ መክፈቻ ጸሎተ ምሕላ እና የብፁዕ አቡነ ቀውስጦስ ትምህርት
- የሐዋሳ ምእመናን ለ4ኛ ጊዜ ለአቤቱታ ወደ አዲስ አበባ መጡ
- የሰበካ ጉባዔ ስብሰባ ተጠናቀቀ፤ ቅ/ሲኖዶስ ተጀመረ
- Ethio-Dejeselamaweyan Leading USA-Dejeselamaweyan ...
- 29ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ እየተካሄደ ነው
- "የሐውልቱ ሥር ቁማርተኞች" ደራሲ፣ ዘሪሁን ሙላቱ በእስራት እና በገንዘብ ተቀጣ...
- አቡነ ፋኑኤል እና ሥራ አስኪያጁ ከሐላፊነታቸው እንዲነሡ የተቀጣጠለው ተቃውሞ ...
- ለአይ.ቲ ባለሙያዎች የአገልግሎት ጥሪ
- መንግሥትን “አበጀህ፣ ጎበዝ” እንበለው ወይስ ገና ነው?
- በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ የአስተዳደር እና ፋይናንስ መዋቅሮች የሐላፊዎች ሹ...
- ክርስትናን በኦርቶዶክስ ዐውደ ምሕረት ስንማረው ነገር ግን በፕሮቴስታንት መንገድ...
- ጠቅላይ ቤተ ክህነት በአስተዳደራዊና መዋቅራዊ ማሻሻያ ዋዜማ?
- አቡነ ፋኑኤል እና ሥራ አስኪያጁ ከሐላፊነታቸው እንዲነሡ የሚጠይቀው የሐዋሳ ምእ...
- በዘሪሁን ሙላቱ ላይ የቅጣት ውሳኔ ለመስጠት ለሐሙስ ተቀጠረ፤ የቅጣት ማቅለያ እ...
- «የአበባ ወር» ወርኀ ጽጌ
- Is the Deje Selam Reporting Good Or Bad?
- ዘሪሁን ሙላቱ የመከላከያ ማስረጃዎቹን አቀረበ፤ ብይኑ ለፊታችን ዓርብ ተቀጠረ
- በሙስናና ኑፋቄ የሚከሰሱት የድሬዳዋ ሀገረ ስብከት ሥራ አስኪያጅ ከሐላፊነታቸው ...
- ሰበር ዜና፦ ብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ወደ አዲስ አበባ ሀገረ ስብከት እንዳይመለሱ የ...
- ቤተ ክርስቲያኒቱ አገራዊ ተደማጭነቷ አደጋ ተጋርጦበታል
- በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እየተፈጸመ ስላለው ጥፋት የምንጽፍበት ምክንያት
- ብፁዕ አቡነ ኤፍሬም የ1.8 ሚልዮን ብር መኪና ተሸለሙ
- መንግሥት የብዙኀን መገናኛዎች በእምነት ተቋማት ውስጥ የተበራከተውን ‹ኪራይ ሰብ...
- የመስቀለኛው ተራራ መስቀላዊ ተልእኮ
- በግሸን ደብረ ከርቤ ማርያም በዓሉ በደመቀ ሁኔታ እየተከበረ ነው
-
▼
October
(63)

Must Read Documents
"1/ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን መንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽ/ቤት/ የመንበረ ፓትርያርክ ጠ/ጽ/ቤት አስተዳዳራዊ እና መዋቅራዊ ችግሮች የዳሰሰ ምልከታ"
አዘጋጅ፡- ልዑልሰገድ ግርማ የጠ/ቤ/ክ/ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ
Click HERE to read.
2/ የቅ/ሲኖዶስ የጥቅምት 2004 ዓ.ም አጀንዳዎች እና ውሳኔዎች፤ እንዲሁም ተያያዥ ዶኩመንቶች:: Click HERE to read and scroll down to (Page 5-20).
አዘጋጅ፡- ልዑልሰገድ ግርማ የጠ/ቤ/ክ/ም/ዋና ሥራ አስኪያጅ
Click HERE to read.
2/ የቅ/ሲኖዶስ የጥቅምት 2004 ዓ.ም አጀንዳዎች እና ውሳኔዎች፤ እንዲሁም ተያያዥ ዶኩመንቶች:: Click HERE to read and scroll down to (Page 5-20).

6 comments:
Please refer MK Web and help us to read
http://www.eotcmk.org/site/images/stories/jornal.JPG
የጥናትና ምርምር ማዕከሉ የመጀመሪያ የጥናት መጽሔቱን (journal) ያስመርቃል።
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት መጽሔት(Journal of Ethiopian Church Studies)” በሚል ስያሜ የመጀመሪያ የጥናት መጽሔቱን መስከረም 29 ቀን 2003 ዓ.ም ያስመርቃል።
መጽሔቱ በባለሙያዎች ታይቶና ተገምግሞ እንዲሁም ሳይንሳዊ የምርምር ዘዴን ተከትሎ በዓመት አንድ ጊዜ የሚወጣ ሲሆን፤ የአሁኑ ዕትም በሦስት ቋንቋዎች የቀረቡ ስምንት የጥናት ጽሑፎችን ይዟል። ከነዚህም ውስጥ ሦስቱ በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተዘጋጁ ሲሆን አምስቱ በአማርኛ ቋንቋ ቀርበዋል።
በአማርኛ የተዘጋጁት ጸሑፎች በአርኪዎሎጂ ቁፋሮ ስለተገኘው የ6ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የሕንፃ ቤተክርስቲያን ፍርስራሽና ኪነ ሕንጻዊ ፋይዳው፣ የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ከግብፅ ቤተክርስቲያን ጥገኝነት ተላቃ በራሷ ፓትርያርክ ለመመራት ስለበቃችበት የረጅም ጊዜ ትግል፣ በዓለም የቅርስ መዝገብነት ስለተመዘገቡት ነገር ግን ብዙም ስለማይታወቁት የሥነ ጽሑፍ ቅርሶቻችን፣ ስለቤተክርስቲያን ንብረቶችና ይዞታዎች የሕግ ጥበቃና ልመናን ለማስቀረት በ1911 ዓ.ም በአንድ የቤተክርስቲያኒቱ ሊቅ የተጠቆሙ መፍትሔዎችን አስመልክቶ የቀረቡ ሐሳቦች ናቸው፡፡
በእንግሊዝኛ ቋንቋ የተጻፉት ደግሞ በቅዱስ ላሊበላ ቤተ ማርያም ውስጥ የሚገኙ ሥዕለ እንስሳ ከመጽሐፍ ቅዱስና ከሥነ ጥንት ጥናት /አርኪዎሎጂ/ ጋር ያላቸው አንድምታ፣ ስለ እንጦጦ ማርያም ሙዚየም አጠቃላይ ዳሰሳ እና በአባ ገሪማ ገዳም የሚገኝ በዘመነ አክሱም የተጻፈ መጽሐፈ ወንጌል የሚሉ ናቸው፡፡
በምርቃት ሥነ ሥርዓቱ ላይ የቤተ ክርስቲያን አባቶች፣ ከጥናትና ምርምር ሥራ ጋር ግንኙነት ያላቸው መንግስታዊና መንግስታዊ ያልሆኑ ተቋማት ተወካዮችና ታዋቂ የምርምር ሰዎች ይሳተፋሉ ተብሎ ይጠበቃል።
Please refer MK Web and help us to read
http://www.eotcmk.org/site/images/stories/jornal.JPG
የጥናትና ምርምር ማዕከሉ የመጀመሪያ የጥናት መጽሔቱን (journal) ያስመርቃል።
በተ/ሥላሴ ጸጋ ኪሮስ
የማኅበረ ቅዱሳን ጥናትና ምርምር ማዕከል “የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ጥናት መጽሔት(Journal of Ethiopian Church Studies)” በሚል ስያሜ የመጀመሪያ የጥናት መጽሔቱን መስከረም 29 ቀን 2003 ዓ.ም ያስመርቃል።
መጽሔቱ በባለሙያዎች ታይቶና ተገምግሞ እንዲሁም ሳይንሳዊ የምርምር ዘዴን ተከትሎ በዓመት አንድ ....
ሰላም ለእናተ ይሁን ወርኅ ጽጌ የጻፋችሁት መልካም ነው ወቅቱን የጠበቀ ስለሆነ ነገር ግን የምሰጠው አስተያየት አለኝ የእመቤታችንን የስደት መጽሀፍ የደረሱት አባ ጽጌ አብርሀም ናቸው ይላል የጻፋችሁት ላይ እኔ ደግሞ የተማርኩት አባ ጽጌ ድንግል ተብየነው እንዲያውም ገዳማቸው በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በግምት ከደሴ 250ኪ.ሜ ይገኛል የኔ ጥያቄ የትኛው ነው ትክክል?
Qale hiwoten yasemalen Amen !!!
YE EMEBETACHEN FEKERA BEREKETA AYLEYEN Amen .
ከድንግል ማርያም በረከት ረድኤት ያሳትፈን
Dejeselam mahlete tgane yederesut aba tega brehane sayhonu aba tega dengle nachew yetarem mekonnen
Post a Comment