(ደጀ ሰላም፤ ሰፕቴምበር 10/2010፤ ጳጉሜን 5/2002 ዓ.ም):- የፌዴራሉ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዘሪሁን ሙላቱ የግል ተበዳዮች ነን ባሉት በእነ ወ/ሮ እጅጋየሁ በየነ የቀረቡበትን የሰው ምስክሮች እንዲከላከል በመወሰን ጉዳዩን ለመመልከት ለመስከረም 14 ቀን 2003 ዓ.ም ቀጠረ፡፡ እስከዚያው ድረስ ተጠርጣሪው ማረፊያ እና ምግብ ወደሚያገኝበት ወደ ቃሊቲ ወኅኒ ቤት ተዛውሮ እንዲቆይ ትእዛዝ ሰጥቷል፡፡
ዘሪሁን ሙላቱ ለፍርድ ቤቱ፣ “በተከሰስሁበት ጉዳይ አንዳችም ማስረጃ አልቀረበም፤ መንግሥትም ጉዳዩን በውል የሚያውቀው አይመስለኝም፤ የመከላከያ ምስክሮቼን ለማቅረብ ከጎኔ የሚቆምልኝ ሰው የለኝም፤ እኔን ለመጠየቅ ወዳለሁበት ፖሊስ ጣቢያ የሚመጡትን ዘመዶቼን እና ጓደኞቼን መታወቂያቸውን እየተቀበሉ ፎቶ ኮፒ በማድረግ እና አድራሻቸውን በመመዝገብ እያስደነበሯቸው ነው” በማለት ቢያስረዳም ዳኛው መልሰው “ቃሊቲ ሊጠይቁህ የሚመጡ ሰዎችን ስም ዝርዝርም አስቀደምህ አስታውቅ” እንዳሉት ተሰምቷል፡፡ በዚህ መሠረት ተጠርጣሪው ከመጪው ሳምንት የአዲስ ዓመት የመጀመሪያ ማክሰኞ በኋላ እስከ አሁን ከቆየበት ከአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ ወደ ቃሊቲ ማረሚያ ቤት እንደሚዘዋወር ተነግሯል፡፡
ከትናንት በስቲያ ጠዋት የዋስ መብቱ ተጠብቆ እንዲለቀቅ በአዲስ አበባ የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት በተወሰነለት መሠረት የተጠየቀውን የ2500 ብር ዋስትና ከፍሎ ከሚወጣበት የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ ጣቢያ በር ላይ በሌላ የፖሊስ ኀይል የተያዘው ዘሪሁን በፌዴራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት በቀረበበት ወቅት በእነ ወ/ሮ እጅጋየሁ ተቆጥረው የመሰከሩበት ዲያቆን ዳንኤል ገብረ ሥላሴ፣ መምህር መሐሪ አድማሱ፣ በጋሻው ደሳለኝ እና ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ ናቸው፡፡ ዲያቆን ዳንኤል “ዘሪሁን ሙላቱ ‘የሐውልቱ ሥር ቁማርተኞች’ መጽሐፍን ዲዛይን ሲያሠራ ተመልክቻለሁ›› ብሎ ሲመሰክር መምህር መሐሪ አድማሱ ደግሞ የመጽሐፉ ረቂቅ በዘሪሁን እጅ ተሰጥቶት ለወ/ሮ እጅጋየሁ ማድረሱን እና ለአምስት ሆነው እንዳነበቡት ተናግሯል፡፡ በጋሻው ደሳለኝ በበኩሉ “ዘሪሁን፣ ገንዘብ ስጠኝ፤ አለበለዚያ እጽፍብሃለሁ” በማለት እንደዛተበት ሲናገር ቀሲስ ሳሙኤል እሸቱ ደግሞ ዘሪሁን መጽሐፉን የማሳተሚያ ብር እንዲሰጠው እንደጠየቀው ለችሎቱ እንዳስረዳ ተዘግቧል፡፡
በዚሁ ዕለት የፍርድ ቤቱ ውሎ በኋላ በችሎቱ የነበሩት ወ/ሮ እጅጋየሁ በየነ፣ ሊቀ ማእምራን ፋንታሁን ሙጬ እና በጋሻው ደሳለኝ “እዚያው እስር ቤት የሚቆይበትን መንገድ እንቅልፍ አጥተን እንደምንም ብለን መፈለግ አለብን፤ ይህ ሰውዬ [ዘሪሁን] በዋስ ከወጣ ከሕዝብም ከመንግሥትም ያጣላናል፤ ከተለቀቀ ያጠፋናል፤ እርሱ እንደው ሕግ አይፈራ!” ሲሉ መደመጣቸው ተመልክቷል፡፡ ይህን ስምምነታቸውን በሚያረጋግጥ አኳኋን ሦስቱ “የግል ተበዳይ ነን” ባዮች ለግለሰባዊ ጉዳያቸው የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከትን መኪና እና ነዳጅ አላግባብ በመጠቀም እና በማባከን ላይ እንዳሉ ብዙዎች በምሬት ይናገራሉ፡፡ ሁኔታውን በቅርበት የሚከታተሉ ታዛቢዎች እንደሚያስረዱት፣ በተለይም ወይዘሮዋ ዘሪሁን ሙላቱን በወኅኒ ቤት ለማሰንበት በሙሉ ጊዜያቸውን እና አቅማቸው የፈጸሙት ድርጊት ‹‹ገንዘብ ሲናገር ፍትሕ ዝም ይላል›› የሚለውን ብሂል ያስታውሰናል ይላሉ፡፡ ለምስክርነት እና ጉዳዩን ለመመልከት ለ‹‹ጉባኤ›› በሚል ከሄደበት ድሬዳዋ ወደ አዲስ አበባ በየቀኑ (እስከ አሁን ድረስ ለተከታታይ ሁለት ቀናት ተመላልሷል) በአውሮፕላን የደርሶ መልስ ጉዞ በማድረግ ላይ የሚገኘው የበጋሻው ደሳለኝ ወጪም ከየት በመሸፈን ላይ እንዳለ ለብዙዎች አጠያያቂ ሆኗል፡፡
የድሬዳዋ ምንጮች ለደጀ ሰላም እንደሚያስረዱት በጋሻው ደሳለኝ በድሬዳዋ ሰፈረ ገነት ደብረ ብርሃን ቅድስት ሥላሴ ገዳም በጠራው ጉባኤ ማንነቱን ዕርቃን በሚያወጣ አኳኋን በካህናት ላይ መረን የለቀቀ ዘለፋ በመናገሩ ካህናት እና ምእመናን በአንድነት ሁኔታውን ለፖሊስ እና ለዐቃቤ ሕግ ማመልከታቸውን፣ የፍትሕ አካሉም ጉዳዩን በማጤን ላይ እንደሆነ ተመልክቷል፡፡ ግለሰቡ ሳይገባው በቆመበት ዐውደ ምሕረት ሲያሰማው ያመሸው ዲስኩር፣ ‹‹ቅዳሴው ቢያልቅበት ቀረርቶ ሞላበት” ይሉት ዓይነት እንደ ነበር በሥፍራው የተገኙ የዐይን ምስክሮች ለደጀ ሰላም አስረድተዋል፡፡
ትናንት ጠዋት ሰፕቴምበር 9/2010፤ ጳጉሜን 4/2002 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከነበረው የፍርድ ቤት ውሎ በኋላ ለሁለተኛ ጊዜ ወደ ድሬዳዋ በአየር ተጓጉዞ የተመለሰው በጋሻው በጥቂት ተባባሪዎቹ አማካይነት ምእመናን በሠርኩ ‹ጉባኤ› ላይ እንዲገኙ በከተማው ሲቀሰቅስ ቢውልም የጠበቀውን ያህል ታዳሚ እንዳልመጣለት ተዘግቧል፡፡ በሁኔታው በመበሳጨትም፣ “ፓትርያርኩ በጥብቅ ስለሚፈልጉኝ ወደ አዲስ'ባ መመለሴ ነው” የሚል ከሀፍረት የመውጫ ሰበብ በተደጋጋሚ በዐውደ ምሕረቱ በመናገር እና በማስነገር ትዝብት አትርፏል፡፡ በጋሻው በከተማው ባካሄደው ቅስቅሳ ጉባኤው ዛሬ እንደሚቀጥል የተነገረ ቢሆንም ትናንት ማምሻውን ከገዳሙ ወጪ ሆኖ በተከፈለ 1500.00 ከሌሎች ሁለት ግለሰቦች ጋራ በሚኒባስ ወደ አዲስ አበባ መመለሱ ታውቋል፡፡ ገዳሙን ለከፍተኛ ወጪ የዳረገውን ይህንኑ ያልተሳካ ‹‹ጉባኤ›› እንዲካሄድ ትእዛዝ የሰጡት ከፓትርያርኩ ለሀገረ ስብከቱ ሊቀ ጳጳስ በተላለፈው መመሪያ መሠረት እንጂ በሀገረ ስብከቱ ሥራ አስኪያጅ ጥሪ እንዳልሆነ ለደጀ ሰላም የደረሰው የማረሚያ አስተያየት ይጠቁማል፡፡
September 10, 2010
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
Blog Archive
-
▼
2010
(305)
-
▼
September
(31)
- የመስቀል ደመራ በዓል መርሐ ግብር ሪፖርታዥ
- የ2003 ዓ.ም ደመራ የኢ.ቲ.ቪ ሪፖርታዥ
- ማስታወቂያ፦ ደጀ ሰላምን በኢሜይል
- የኢሉ-አባ-ቦራው የአክራሪዎች ችግር እና ሃይማኖታዊ ምልከታዎቹ
- ራሳቸው ሳይታመኑ ስለመታመን ለሚያስተምሩ በሙሉ!!
- ስለ ሕገ ወጥ ሰባክያን እና ዘማርያን የወጣው መመሪያ ግልጽነት እንደሚጎድለው እ...
- በገቺው የአክራሪ ሙስሊሞች ሁከት 13 ግለሰቦች በቁጥጥር ሥር ዋሉ
- የኢሉአባቦራው የአክራሪዎች ችግር ከአንድ ቀበሌ በላይ የተዛመተ ችግር ነው
- በስብከተ ወንጌል መስፋፋት እና መጠናከር ላይ ያተኮረ ዐውደ ትምህርት ተጀመረ
- የገቺ ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተ ክርስቲያን ምእመናን በአክራሪ ሙስሊሞች...
- ቤተ ክህነቱ ያጣው የቤተ ክህነቱ ሰው
- አቡነ ፋኑኤል ከሐላፊነታቸው እንዲነሡ ተጠየቀ
- በሐዋሳ ገብርኤል ሊካሄድ የነበረው የሰበካ ጉባኤ ምርጫ በሕዝበ ክርስቲያኑ ተቃው...
- መንግሥት ከጳጳሳቱ ጋራ የሚያደርገው ውይይት እንደቀጠለ ነው
- የደቡብ ክልላዊ መንግሥት ባለ ሥልጣን አቡነ ፋኑኤልን አስጠነቀቁ፤ ያሬድ አደመ ...
- መንግሥት ከፓትርያርኩ እና ከጳጳሳቱ ጋር ምሥጢራዊ ስብሰባ አካሄደ፣ ማሳሰቢያም ...
- መንግሥት “በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም” ተባለ እንጂ ሃይማኖት ላይ ወንጀል ሲፈጸ...
- “አዲስ ልብና አዲስ መንፈስ ለእናንተ አድርጉ” /ሕዝ 18፥31/
- ዘሪሁን ሙላቱ ወደ ቃሊቲ ወኅኒ ቤት ወረደ
- ሁለቱ ማኅበራት:- "የቅድስት ሥላሴ መንፈሳዊ ኮሌጅ ምሩቃን ማኅበር" እና "የአ...
- ማኅበረ ቅዱሳን ‹የአገልግሎት ስልት ለውጥ› እንደሚያስፈልገው አመለከተ
- በዋስ እንዲለቀቅ የተወሰነለት ዘሪሁን ዳግመኛ ተይዞ ፍርድ ቤት ቀረበ
- የሐምቡርግ ኪዳነ ምሕረት ቅዳሴ ቤት ተከበረ
- ዘሪሁን ሙላቱ በ2500 ብር ዋስ ተለቀቀ
- በለንደን በሺዎች የሚቆጠሩ ምዕመናን ቀልብን የሳበው የስብከተ ወንጌል ጉባኤ
- የኢትዮጵያ ታሪካዊ ቅርሶች በአደጋ ውስጥ ናቸው ተባለ
- ያሬድ አደመ በኮፒ ራይት ጥሰት ሊከሰስ ነው
- ሐውልቱን በመቃወም የተጠረጠሩት የቦሌ መድኃኔ ዓለም ካቴድራል ጸሐፊ ከቦታቸው ተ...
- “የትኛው ሰባኪ፣ የትኛው ዘማሪ እዚህ አደባባይ መቆም እንዳለበት ወስነን እስክን...
- ፍርድ ቤቱ በዘሪሁን ሙላቱ ላይ ሦስተኛ ቀጠሮ ሰጠ
- ማስታወቂያ፦ የድረ ገጽ አድራሻ ለውጥ
-
▼
September
(31)
8 comments:
Greetings in the name of God, the Almighty.
I'm just a neutral reader of your site. But when I see the way you are writing about some individuals, it looks that you are not telling us the truth rather your biased opinion. It reminds me of the struggle between Derg and Woyane or Woyane and Shabia and thier respective fabricated allegations of one on the other on the media owned by each of them.
lehulachehum mihretun yawredilachehu
Kesis HaileSelassie
to mesfin(kesis hailesilase)
i don't think you are neutral. this site is posting the truth. no affiliation or personal attitude. please tell us which one is biased opinion. we people know better than whom inside the church(betekihinet)what tehadiso is doing.keep it up Dejeselams. God bless you with his mother St. merry
so called kesis hailesilassie!
Can u mention the information that is biased?
Deje Selam is informing only the true Tewahedo believers and surely dosn't satify at all those who r not truely Tewahedo.
+++
በስመ ሥላሴ ትቀጠቅጥ ከይሴ
እንደኔ እንደኔ ዘሪሁን ና በጋሻዉ የአንድ ሳንቲም ሁለት ገጽታ ናቸዉ:: አስተዉላችኋል:: ነገሩ እንዲህ ነዉ:_
፩/ሁለቱም የቤ/ያናችን ጠላቶች ናቸዉ::እምነቱምሆነ እዉቀቱ የላቸዉም
፪/ሁለቱም ያለትምህርት ሜዳላይ የተሰጣቸዉ ስልጣን ይዘ ዋል::
፫/በጋሻዉ የመስቀሉ ሥር ቁማርተኞች ሲጽፍ; ዘሪሁን ደግሞ መልስ አዘጋጀ ተብሎ ከሜዳ ተጠራ የቤ/ያንን አባት ዘለፈ በለመደዉ አንደበቱ የሐዉልትን ሥር ቁማርተኞች ጻፈ እርሱም ግን ከስሩ አለበት:: ሁለቱ በቤተ ክህነቱ ተጠግተዉ ቤ/ያንን አዋርደዋል::ዘልፈዋል:: በጽሁፎቻቸዉ ሆነ በቃል አባቶችን ተሳድበዋል::በጋሻዉ በሰሞኑ በድሪደዋ ጉባኤ ላይ ካህናት አባቶችን እንደተሳደበዉ::
፬/ሁለቱም በሆዳቸዉ ለሆዳቸዉ ነዉ የሚኖሩት:: የተሻለ ካገኙ አይምሩም::
፭/ሁለቱም የቅድሥት ሥላሴ ቲዎሎጅ ተበክሎ በነበረ ዘመን የጨረሱ ናቸዉ:: ይህ ሁኖ ሳለ ቤተክህነቱ ሰዉ አገኘሁ ብሎ ቤ/ያንን ያዘልፋሉ:ያዘርፋሉ:: አሁንም ጠብቁ በጋሻዉ ይቀጥላል::
የቤ/ያን አባቶች እባካችሁ ከስራቸዉና ከፍሪያቸዉ ዕወቁአቸዉና አታቅርቧቸዉ:: ቤ/ያንን አታስደፍሯት::
ረዴተ እግዚአብሔር አይለየን::
Thank you for the information you shared us. Somebody commented on Begashaw and Zerihun saying " huletum ye qidist Silassie tewoloji tebekilo benebere zemen yecheresu nachew." Though each of us has a right to give our comments freely, but we have to do it in truth and a manner that may construct a reader's life. Begashaw dismissed from the Holy Trinity College when he was a second year student. During his two years study he learnt only the common courses. He never studied the main theological subjects.Hence we have not to call or consider him as a graduated from the Holy Trinity Theological College.
Beside this, we have not to blame the college saying "ye Qidist Silassie College tebekilo benebere...." How we are sure to say "tebekilo?" Every institute has its own weak and strong sides. There were many heretics from the school of Alexandria. Could we neglect the strength of that school irritating by the danger of those heretics? Never!!!! In the same manner there are a number of faithful and strong graduates from the Holy Trinity Theological college till now. So it is not fair and ethical to call and to lebel the college " yetebekele, tebekele". Let us differentiate between the persons and the college. The college, though it has some administrative problems that needs our church members positive and practical concerns, is doing its part to train students in different theological fields. So, let us not generalize as if the college is distorted.
+++
The 4th Anonymous please I am not insulting our collage. I stated the time when the collage was faced problem as you mentioned. My brother see also the following information from his profile from his facebook adress "Me
Basic Info Sex: Male
Birthday: April 23, 1980
Interested In: Women
Men
Looking For: Friendship
Political Views: Revolutionary Democracy
Religious Views: Orthodox
Work and Education
Employers Private Business
College Trinity College, Addis Ababa
High School Dilla Senior Secondary School '00
Likes and Interests
Other Roses ♥ Dreams, AVITRAV AIR TOUR, Megabe Haddis Begashaw Dessalegn, Entoto Kidanemeheret Church, ETHIOPIAN UNITY- HUMANITY BEFORE ETHNICITY, Meseret Defar Roses ♥ Dreams
Contact Information
Email begashawdessalegn@yahoo.com"
God bless us
Dear last Anony;
Although I'm not saying Kidist silassie college is distorted, I would say it has lots of institutional and academical problems. This is reflected on the behavior and the contribution of its most graduates. Most of the graduates are not behaving even as Christians. They are professionals. They are not leaving up to the Gospel they are preaching. We are not witnessing significant contribution of the graduates specially those serving in main cities like Addis and abroad. Most of them are running after pride and money. We need more humble and determined servants.
When I say DS is posting biased opinions what I mean is, eventhough you are trying to protect our church from any adversaries,you are doing it by making one-sided reports on incidents. You extremely condemn those individuals who are not your members/members of MK/ & extremely praise those who are affilated with you or MK. I support what MK is doing for our church with some reservations & comdemn what some individuals are doing against the church. But when you post a report/article on any issue, you better make it neutral and balanced. Everyboody in the church has his own weakness but it would be constructive if we comment each other in a positive and unbiased way.
May the intercession of St. Mary & the Saints be with us.Amen.
Kesis HS
Post a Comment