አዲስ አበባ፤ ጥቅምት 19 ቀን 2002 (ኢ.ዜ.አ) - ለአምስት ቀናት የሚቆይ የአፍሪካ ወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ህብረት ጉባኤ አዲስ አበባ ውስጥ ዛሬ ተጀመረ፡፡ ኢትዮጵያ የወወክማን ጉባኤ ስታስተናግድ ይህ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው፡፡ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የስብሰባ ማእከል የተጀመረውን ጉባኤ በንግግር የከፈቱት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ ብጹህ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ወጣቶች የወደፊቱ ህይወታቸው ብሩህና ተስፋ የተሞላበት እንዲሆን በመቻቻልና እርስ በእርስ በመደጋገፍ መስራት ይኖርባቸዋል ብለዋል፡፡
ወጣቶች ነገ እንዲኖራቸው ለሚሹት መልካም ህይወት ዛሬ ላይ ቆም ብለው በእርጋታና በጥንቃቄ መራመድና ማሰብ እንዳለባቸው የመከሩት ብጹእነታቸው የአፍሪካ የወደፊት ተስፋዋ የተማሩና በስነ ምግባር የታነጹ ወጣት ዜጎቿ መሆናቸውንም ተናግረዋል፡፡
የወጣቶችና ስፖርት ሚኒስትር ወይዘሮ አስቴር ማሞ እንዳሉት በኢትዮጵያ በሚካሄዱ ማህበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ላይ የወጣቶችን አቅም ለማጎልበት እና ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ ለማስቻል መንግስት ብሄራዊ የወጣቶች ፖሊሲ ቀርጾ እየተንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ በወጣቶች ዙሪያ የቀረጻቸውን ፖሊሲዎች ተግባራዊ ለማድረግም ፖለቲካ፣ ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮችን የተመለከቱ የወጣቶች የልማት ማእቀፍ አዘጋጅቷል፡፡
ባለፉት ሁለት አመታት ብቻ እንኳ በተለያዩ መስኮች ከ72 ሺህ በላይ የወጣት ድርጅቶች በመላው አገሪቱ ተመስርተዋል፡፡
እንዲያም ሆኖ ወጣቶች ያሉባቸው ሁሉን አቀፍ ችግሮች በመንግስት ጥረት ብቻ ይፈታሉ ብለው እንደማያስቡ ገልጸዋል፡፡ እናም ሚኒስትሯ የሁሉም አካላት የተባበረ ጥረት እንደሚያስፈልግ ጠቁመዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማህበር /ወወክማ/ ፕሬዚዳንት ዶክተር ብርሃኑ ታደሰ በበኩላቸው ማህበሩ በ1952 በቀዳማዊ ሃይለ ስላሴ ዘመነ መንግስት መቋቋሙን ገልጸዋል፡፡ ማህበሩ በንጉሱ ጊዜ የሚያደርጋቸው እንቅስቃሴዎች መልካም የሚባሉ እንደነበሩ ያስታወሱት ፕሬዚዳንቱ የደርግ መንግስት ማህበሩን ሙሉ በሙሉ እንዳይንቀሳቀስ በማገዱ የማህበሩ እንቅሰቃሴ ተቋርጦ መቆየቱን ገልጸዋል፡፡
ማህበሩ ዳግም ተመስርቶ መንቀሳቀስ የጀመረውም እ ኤ አ ከ1992 ጀምሮ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም 15 ሺህ አባላት እንዳሉት ተናግረዋል፡፡ በአራት ክልሎች ዘጠኝ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶች አሉት፡፡
ፕሬዚዳንቱ እንዳሉት ዛሬ አዲስ አበባ ውስጥ የተጀመረው የአፍሪካ ወወክማ ህብረት ጉባኤ ዋነኛ አጀንዳም ወጣቱ ትውልድ የወደፊቱ አገር ተረካቢ በመሆኑ ከተመልካችነት ወደ ተዋናይነት እንዲሸጋገር ለማስቻል ሲሆን በየአገሩ ያለውን ወቅታዊ ሁኔታ በመገንዘብ መጪውን ጊዜ ለመቀየስ በሚያስችሉ ሁኔታዎች ላይ ለመምከር ነው፡፡
ወወክማ በህብረተሰቡ ውስጥ ዝቅተኛ ህይወት ያላቸውንና ጉዳት የደረሰባቸውን የህብረተሰብ ክፍሎች በተለይም ወላጆቻቸውን በሞት ያጡ ህጻናትን፣ ሴተኛ አዳሪዎችን፣ ጎዳና ተዳዳሪዎችን ምንም አይነት የፖለቲካ፣ የሃይማኖትና የብሄር ልዩነት ሳያደርግ እገዛ በማድረግ ላይ እንደሆነም ፕሬዚዳንቱ ተናግረዋል፡፡
የኢትዮጵያ ወወክማ 124 አባል አገራት ያሉት የአለም አቀፉ ወወክማዎች ህብረት አባል ነው፡፡
October 29, 2009
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
Blog Archive
-
▼
2009
(275)
-
▼
October
(34)
- በቅዱስ ዮሐንስ ጠበል ከሆድ ውስጥ ወፍ ወጣ
- ጥያቄ፦ "ቅዱስ ሲኖዶስ ስለ ማኀበረ ቅዱሳንስ ምን ወሰነ? የአዲስ አበባ ሀ/ስብ...
- የአፍሪካ ወጣት ወንዶች ክርስቲያናዊ ማህበር (ወወክማ) ሕብረት ጉባኤ አዲስ አበ...
- ደጀ ሰላማችን ሰላም እንድትሆን!
- የአቡነ ሳሙኤል ልማት ኮሚሽን ላይ መሾም ምን አንድምታ አለው?
- ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የEthiopia zare ሪፖርታዥ፦ “የኢትዮጵያ ኦርቶ...
- ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የሪፖርተር ጋዜጣ ሪፖርታዥ:- "የቅዱስ ሲኖዶሱ ጉባዔ...
- ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ ሳይሰበሰብ ዋለ፤ ነገ ይቀጥል ይሆናል
- የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ዓለም አቀፋዊ የምእመናን ማሕበር መ...
- The Ongoing Crimes of “Patriarch Abune” Paulos ag...
- ኢህአዴግና የሃይማኖት ፖለቲካ
- ቅ/ሲኖዶስ በብፁዕ አቡነ ሳሙኤል ዝውውር ላይ የጀመረውን ውይይት ሳይፈጽም ቀረ
- ቅ/ሲኖዶስ በሁለት አጀንዳዎች ላይ የጀመረውን ውይይት ሳይፈጽም አሳደረ
- ቅዱስ ፓትርያርኩ “ይቅርታ አድርጉልኝ አባቶቼ፤ ሰዎች አሳስተውኝ ነው” አሉ፤
- ቅ/ሲኖዶስ የሰንበት ት/ቤቶች ማ/መምሪያ በሊቀ ጳጳስ እንዲመራ ወሰነ
- Mahibere Kidusan, The Next Target?
- የለንደን ቅ/ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለቅ/ሲኖዶስ ጥሪ አቀረበ
- ኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት - "በቤተክርስቲያኗ አባቶች መካከል ተፈጥሮ የነበረው ...
- (ሰበር ዜና) መንግሥት አባቶችን አስጠነቀቀ ተባለ
- "ቤተክርስቲያን በልማቱ መስክ የምታደርገውን ተሳትፎ ይበልጥ አጠናክራ ትቀጥላለች...
- የቅዱስ ሲኖዶስ ጉባዔ ነገ ይጀመራል፣ አባቶች ምንም እንዳይናገሩ እየተነገራቸው ...
- ለኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ: Petition
- የጠቅላይ ቤተ ክህነት የሰበካ አጠቃላይ ሀገር አቀፍ ስብሰባ ነገ ይጀመራል፤ ቅ/...
- “እጅ ስጡ ለእግዚአብሔር”:- የሽመልስ አበራ መዝሙር
- (ሰበር ዜና)፦ የፓትርያርኩ የወንድም ልጅ በፖሊስ ታሰረ
- ብፁዕ አቡነ ማትያስ ቀጣዩ አቡነ ሳሙኤል እንዳይሆኑ!!!! የወ/ሮ እጅጋየሁ (ኤ...
- ተሐድሶና የተሐድሶዎች ነገር
- Global Muslim population hits 1.57 billion, Ethio...
- Catholic Cardinal Stresses Dialogue With Orthodox ...
- Ethiopian Patriarch on Faith in Africa
- “መንግሥትን የጋበዘው ማኀበረ ቅዱሳን ነው” የሚለው የአባ ሰረቀ “የአብዬን ወደ...
- በማኀበረ ቅዱሳን ጉዳይ “አዲስ ነገር” የዘገበው
- Before Lucy came Ardi, new earliest hominid found ...
- አለቃ አያሌው ታምሩ መስከረም 21 ቀን 1990 ዓ.ም ምን ብለው ነበር?
-
▼
October
(34)
5 comments:
Guys r u confused or trying to confused us why do u say leke-papas for our patriarke /gudoche gude endatametulen/
አገር ቤት--በተለይም ባዲስ አበባ--ያላችኹ እውነተኞች የተዋሕዶ ልጆች፦
እባካችኹ፣ እባካችኹ፤ የማበሩን ደንብና ሥራት አጥንታችኹ ቶሎ ቶሎ ተመዝገቡ እና አባላት ኹኑ። አመራር ደረጃ ላይም ለመድረስ ሞክሩ። ኢትዮጵያ ምድር ላይ "ክርስቲያን" በሚል ስም ለሚቋቋም ማንኛውም ዐይነት ነገር ብቸኛ ባለቤቶች መኾናችን ቢቀር ግንባር ቀደም ተዋናይ መኾን ያለብን እኛ መኾናችንን አትዘንጉ። "ባላዋቂ ቤት እንግዳ ናኘበት" የሚለው አባባል በኛ ላይ መፈጸሙ ያብቃ እስኪ! (በመጽሐፍ ቅዱስ ማበር እና በመሳሰሉት የሚፈጸመውን አስቡት)
እውነቱን ከተናገርኹ፦ በርግጥ እንዲኽ ያለው ጥርቅም ባይመሠረት ደስ ባለኝ! አንዴ ከኾነ ዘንድ ግን ዛሬ አኩርፈን ዳር ዳር ስንል ነገ በሚፈጠረው ችግር ከመቊሰል እማኽሉ ገብቶ ጕዳቱን እየቀነሱ ጥቅሙን ማሳደግ ስለሚሻል ነው ከላይ ያለውን አስተያየት የሰጠኹት። "እንደእባብ..." በሚለው መመሪያ መሠረት...
Wakwoya Dhuga commented on your note "ስለ ቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ የሪፖር&#...":
"ልበ ደንዳናው አባ (አቡነ አላልኩም)ጳውሎስ እና ሰውን የማያፍሩ፤ እግዚአብሔርንም የማይፈሩት ማፍያ ጓደኞቻቸው ርብርብ ቅዱስ ሲኖዶሱን መከፋፈል ሳይቻለው ቀርቷል፡፡ በአቡነ ሳሙኤል ጉዳይ ላይ ሰላሳ ሰባት ሊቃለ ጳጳሳት በድምጽ ብልጫ የአባ ጳውሎስን ውሳኔ መሻራቸው በራሱ የጥቅምቱ ሲኖዶስ ጥንካሬ ተደርጎ ሊታይ ይችላል፡፡ በመሠረቱ ከንቱ ውዳሴ (ከፍተኛ የሆነ የክብር ፍላጎት) የእለት ምግብ ያህል ለሚርባቸው እና፤ ፍቅረ ንዋይ ላሳወራቸው አባ ጳውሎስ የአቡነ ሳሙኤል በዕርዳታ ኮሚሽን መመደብ ሊያሳብዳቸው ቢደርስ ብዙም አይደንቅም፡፡ የለመደ ረጅም እጃቸውን ወደ ኮሚሽኑ የገንዘብ ቋት ሲሰዱ በቅርቡ ዳግም ግጭት ላለማገርሸቱ እርግጠኛ መሆን አይቻልም፡፡
እጅግ የሚገርመው ጉዳይ፤ አባ ጳውሎስ ቀዱስ ሲኖዶሱን ለማሞኘት እና የውሳኔያቸው ተገዢ ለማድረግ ‹‹በእኔና በአቡነ ሳሙኤል መካከል ሰው ነው የገባው›› ሲሉ መደመጣቸው ነው፡፡ ለመሆኑ የፓትርያርኩን ልብ ወደፈለው አቅጣጫ እየነዳ ገየሚጫወትበት እና ከቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ በላይ ሆነው ያ ሰው ማነው፤ ጠንቋዩ ጌታቸው ዶኒ፤ አለሌው ያሬድ፤ ጅቡ ዘሪሁን፤ ጋለሞታዋ እጅግጋየሁ፤ ከርሳሙ ወለወደ ሩፋኤል ወይስ ሌሎች የማናውቃቸው ! ለነገሩ በፓትርያርኩ ዙሪያ የተኮለኮሉት እኮ ለሆዳቸው እነጂ ለመንጋው የማይገዳቸው ቆብ ስለደፉ ‹‹የመነኮሱ›› የመሰላቸው፤ ልባቸው ያበጠ፤ የዚህ አለም ነውረኞች እነኳን የማይደፍሩትን የእግዚአብሔርን ቤተመቅደስ በመዳፈር ወደር ያልተገኘላቸው የዚህ ዘመን ጉዶች (በገድለ አበው ጸሊም አርጋብ ተብለው የተነገረላቸው) ናቸው፡፡
እንኳን ልበ እውሩን አባ ጳውሎስን ዘረኛውን እና የገዛ የትግል ጓደኞቹን ሳይቀር ለገንዘብና ለሥልጣን ሲል በማሰር እና በመግደል የሚታወቀውን መለስ ዜናዊን ‹‹አንተ ውእቱ ቴዎድሮስ … ዘተብህለ በእነቲአከ›› (ከምሥራቅ ይነሳል ተብሎ ተነገረልህ ቴዎድሮስ አንተ ነህ) በማለት የሰማዩን ሳይሆን የምድሩን በማሞገስ እና በማወደስ የዚህን ዓለም ረብ በመመኘት ወደር ያልተገኘላቸው የቤተክህደት ‹‹ሊቃውንት›› ነገ ደግሞ ምን እንደሚያሰሙን እንጠብቃለና!
‹‹… አንተ ከእግዚአብሔር ፍርድ የምታመልጥ ይመስልሃልን? ወይስ የእግዚአብሔር ቸርነት ወደ ንስሐ እንዲመራህ ሳታውቅ የቸርነቱንና የመቻሉን የትዕግሥቱንም ባለጠግነት ትንቃለህን? ነገር ግን እንደ ጥንካሬህና ንስሐ እንደማይገባ ልብህ የእግዚአብሔር ቅን ፍርድ በሚገለጥበት በቍጣ ቀን ቍጣን በራስህ ላይ ታከማቻለህ።›› ሮሜ.2:1-5"
To dear Sisters and Brothers of Orthodoxiawuyan let leave tesfa to be a member of YMCA.
Yiqoyen
Dear deje selam! Do you have any information about the today´s meeting of the Holy Synod? You have written about the transfering of Abune Samuel to development commission of EOTC.
Could you answer the following my questions please?
1.Who is appointed as an archbishop to A.A Hagere Sebket?
2.What kind of decision is passed to solve the problem of Mahebere Kedusan?
It was one of the expected agendas.
Post a Comment