(ደጀ ሰላም፤ ጁላይ 18/2009)
(አቤል ዘቀዳማዊ እንደጻፈው)
እንግዲህ የዛሬው የቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ የእናተው ዘገባ ካየሁ በኋላ፤ ከራሴ ጋር ብዙ ጥያቄዎች በማንሳት ተከራከርኩና ህገ ቤተ ክርስቲያንም ማገላበጥ ጀመርኩ ።
ከጥያቄዎችም መካከል፦
• የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የቤተ ክርስቲያኒቱን ሕግ ያውቁታል ወይስ አያውቁትም ?
• የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ያለባቸው ኃላፊነትስ በትክክል ተረድተውታል ወይ?
• ከዚህ በኋላስ ሊቃነ ጳጳሳቱ በምን ሞራል ነው ልጆቻቸው መባረክ የሚችሉት?
• ለቤተ ክርስቲያኒቱ ህግና ሥርዓት ተቆርቃሪዎች እውነተኞቹ ነገር ግን በቁጥር ትንሽ የሆኑት የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት እንዴት ከሕዝበ ክርስቲያኑ ጋር ሊገናኙ ይችላሉ?
እስቲ ቅዱስ ፓትርያርኩም ሆነ ብዙዎቹ የቅዱስ ሲኖዶስ አባላት የማይቀበሉት ህገ ቤተክርስቲያን ስለ ፓትርያርክ ስልጣንና ተግባር ምን ይላል? ለዚሁ ጥያቄ መልስ ለማግኘት በራሳቸው በቅዱስ ሲኖዶስ አባላት ተቀባይነት ያላገኘውን ህገ ቤተክርስቴያን ካነበብኩት ላካፍላችሁ
1. ፓትርያርክ ተጠሪነቱ ለቅዱስ ሲኖዶስ ነው (ሕገ ቤተክርስቲያን 1991)
2. ፓትርያርክ የቅዱስ ሲኖዶስና የቋሚ ሲኖዶስ ስብሰባዎችን ይመራል
3. በቅዱስ ሲኖዶስ መመሪያ ለብፁዓን ጳጳሳት የሊቀ ጵጵስና መዓረግ ይሰጣል
4. ለታላላቅ ገዳማት አበ ምኔቶችና በሀገረ ስብከቱ ለተመረጡ ገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች የመዓረግ ስም ይሰጣል
5. ከቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጡና የተላለፉ ሕጎች፤ ደንቦች፤መመሪያዎችና ልዩ ልዩ ውሳኔዎች በተግባር መዋላቸውን ይከታተላል
የፓትርያርክ ከስልጣን መውረድስ ህገ ቤተክርስቲያን ምን ይላል?
ፓትርያርኩ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ላይ ከተሾመ በኋላ የተቀበለውን ኃላፊነት በመዘንጋት፦
• የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን ትምህርተ ሃይማኖት የሚያፋልስ፤ቀኖና ቤተክርስቲያንን የሚያስነቅፍ ተግባር ፈጽሞ ከተገኘ
• በፍትህ መንፈሳዊ አንቀጽ አምስት ከቁጥር 172 እስከ 208 በተደነገገው መሰረት በደለኛ ሆኖ ከተገኘ
• በኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በ1991 በወጣው ሕገ ቤተክርቲያን አንቀጽ 13 ንዑስ አንቀጽ ሰባት መሰረት በተሾመበት ቀን የገባው ቃለ መሐላ ያልጠበቀ እንደሆነ
በአጠቃላይ ታማኝነቱ፤መንፈሳዊነቱና አባትነቱ በካህናትና በምእመናን ዘንድ ተቀባይነት ያጣ ሆኖ ቤተክርስቲያንን የሚያስነቅፍ መሆኑ በትክክል ከተረጋገጠ ከስልጣኑ ይወርዳል። በሱ ምትክም ሌላ ተመርጦ ይሾማል። ፓትርያርክ እስኪሾም ግን ዐቃቤ መንበረ ፓትርያርክ ይመረጣል። የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ያወጣው ሕገ ቤተክርስቲያን 1996 አንቀጽ 16
ሕገ ቢተክርስቲያን ይህ ሆኖ ሳለ የአሁኑ ፓትርያርክ ከላይ የተጠቀሱት ህጎች ሁሉ እያፈረሱ፤ እኛም እያየነቸው የቅዱስ ሲኖዶሱም አባላት እያዩዋቸው እስካሁን ድረስ በዝምታ ታልፈዋል። ከዚ በኋላስ መፍትሔው ምንድ ነው? ተስፋ ቆርጦ መተው ወይስ ከጥቂቶቹ ለሕገ ቤተክርስቲያን ተቆርቋሪ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት ጋራ አይዞዋችሁ እኛም ከጎናችሁ ነን በማለት መስራት? መልሱን ለውድ ደጀ ሰላማውያን/ት በመተው አንድ ነገር ግን ላሰምርበት እወዳለሁ የኢ/ኦ/ተ/ቤተክርስቲያን በፓትርያርክ ላይ ፓትርያርክ የሚል ህግም ደንብም የላትም።
እግዚአብሔር ተዋህዶ ሃይማኖታችን ይጠብቅልን!!! አሜን
July 18, 2009
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
Blog Archive
-
▼
2009
(275)
-
▼
July
(75)
- ጠቅላይ ቤተ ክህነት “አዲስ ነገር ጋዜጣን” ከሰሰ
- +++++++ - - - - - - ???? ?? About Mahibere Kidusa...
- "ኘትርክናው ከሆነላችሁ መልካም" ግብጻውያን
- ለቅዱስነትዎ ይድረስ
- ‘‘ለሀገር ፍቅር ሬዲዮ" አዘጋጅ ለአቶ ንጉሤ የተሰጠ መጠነኛ አስተያየት
- በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚኒያፖ...
- ርዕሰ አንቀጽ፦ “ደጀ ሰላም” የማን ናት?
- እስከ ጥቅምት ቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ ምን እንሥራ?
- አቡነ ቄርሎስ የቤተ ክህነት ግቢን ለቀቁ
- ፓትርያርኩ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ኃላፊዎችን ሰበሰቡ፤ መመሪያ ሰጡ
- ጉዞ ወደ እስክንድርያ በድጋሚ? እንዴት ተደርጎ!!!
- ‹‹ማርቆስ አባታችን እስክንድርያ እናታችን›› ብለን ወደ ቀደመው ድንኳን እንሂድ...
- ድንቄም ተቆርቋሪ
- የወቅቱን የቤተ ክርስቲያን ችግር አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ጥሪ አስተላለ...
- የቤተ ክህነቱ ማፊያ ቡድን አሁንም አልተያዘም፤ ውንብድናው ከተፈፀመ ሳምንት ሆ...
- “ብሩን መልስና ተመለስ ወደ እውነት” (ለንጉሴ ወ/ማርያም)
- የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ዝግጅት በቅንጭቡ፤ ኪነ ጥበባዊ ቅንብር በዳን
- ጳጳስ
- የማፊያው ቡድን ድምጽ ንጉሴ ወ/ማርያም ፓትርያርኩ “ገንዘብ በመቀበል ጵጵስና ይ...
- የሎንዶን ደ/ሰ/ቅ/ማርያም ሰበካ ጉባዔ በአባቶች ላይ የተፈጸመውን ወንጀል አወገ...
- ሰበር ዜና (Breaking News) መንግሥት “ፓትርያርኩን ተቃወሙ” ያላቸውን ...
- “ፓትርያርኩ አሸነፉ” መባሉን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ተቃወሙ፤ ሌሎች ደገፉ...
- የማፊያው ቡድን ድምጽ በአሜሪካ “ማጥቃት” ጀመረ፤ የቁልቢ ብር ሥራውን እየሠራ ...
- አንዳንድ ነጥቦች ስለ ሕገ ቤተ ክርስቲያን
- ስለ ቅ/ሲኖዶስ ስብሰባዎችና ውሳኔዎች ሒደት የአዲስ ነገር ጋዜጣ ልዩ ሪፖርታዥ
- Comments To Be Moderated
- የግርግሩ ፍጻሜ ማግሥት
- የሁለቱ ወር የቅ/ሲኖዶስ ውጣ ውረድ ሲጠቃለል፤ ሪፖርታዥ
- ስውሩ የአቡነ ጳውሎስ እጅ ድል አደረገ፤ ስብሰባው “የፓትርያርኩን አቋም በመደገ...
- People Who Attacked Ethiopian Bishops Are not Arre...
- የቤተ ክህነቱ ማፊያ ቡድን አሁንም አልተያዘም፤ የመንግሥት ደህንነቶች ሳይኖሩበት...
- አባቶች አካላዊ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ታወቀ
- (ሰበር ዜና፣ Breaking News) ብፁዓን አባቶች ላይ አደጋ ተጣለ
- የሥራ አስፈጻሚው ዕገዳ ተነሣ
- በመንግሥት አደራዳሪነት ዝግ ስብሰባ እየተደረገ እንደነበረ ታወቀ
- ሪፖርተር ጋዜጣ የተሳሳተ መረጃ እያሰራጨ ነው
- Question And Answers About the Holy Synod Meeting:...
- Challenge the Idea Not The Person: How Deje Selam ...
- ሰበር ዜና (Breaking News):- አባቶች በመጨረሻ ተፈራረሙ!!!! የፈረሙ...
- ለአጋእዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ በዓል እንኳን አደረሳችሁ
- የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ ዛሬ ማክሰኞም ይቀጥላል
- አቡነ ገብርኤልና አቡነ ሙሴ ለምን ያውካሉ?
- ይህ ሁሉ ስለምን ደረሰብን? ምንስ እናድርግ?
- ስብሰባው ያለምንም ውሳኔ ተበተነ
- ቅዱስ ሲኖዶስ በፓትርያርኩ ሰብሳቢነት እየተነጋገረ ነው
- የጥብዐት ቁልፍ - Key To Resolution
- የብፁዕ ወቅዱስ ሥልጣን “ልጓም እንዲበጅለት” የሚፈልጉ ወገኖች እነማን ናቸው?
- “ቸር ወሬ ያሰማን”
- ግብር አልባ ለሆነው የሥልጣን ወንበር ጥበቃ የተደረገ ሞት ሽረት
- መንግሥት አቋሙን ገለጸ፣ አቡነ ሳሙኤል ተለቀቁ፣ ስብሰባው ይቀጥላል
- በተዋሕዶ ነን ወይ ?
- ምርጥ ንግግሮች ስለ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያናችን ጉዳይ
- እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ፥ ልብህም ይጽና፤
- ሰበር ዜና (Breaking News) እና ሪፖርታዥ፦ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በአ...
- ወ/ሮ እጅጋየሁ ወይስ የዘመኗ ኤልዛቤል?
- ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔው ላይ ሳይፈርም ቀረ፤ ጋዜጠኛው ተደበደበ
- ቅ/ሲኖዶስ የፓትርያርኩን “ሁሉን አቀፍ ሥልጣን” ገፈፈ፣ “እንደራሴ” ሾመ
- ደጅሽ ላይ ቆሜ እጠራሻለሁ
- በሃይማኖት ጣልቃ አለመግባት እስከ ምን?
- የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ ቀጥሏል
- “ማኔ ቴቄል ፋሬስ” (ትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ 5) “እግዚአብሔርን የማያውቁ የእ...
- ቅ/ሲኖዶስ ዛሬም ሳይሰበሰብ ቀረ
- “የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ያለ ፓትርያርኩ መሪነትም ቢሆን ይካሄዳል” (ቋሚ ሲኖዶ...
- "ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊነት የሚጠበቅብንን ሁሉ በማድረግ እንትጋ"
- በዘመናት መካከል የተገኘ ዘመን የማይሽረው ልዕልና
- አስቸኳዩ የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ እንዳይካሄድ ከፓትርያርኩ ተቃውሞ ቀረበ
- ግልጽ ደብዳቤ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በእስዎም በኩል ለቤተ ክርስቲያኗ ሲ...
- አያሌው ግራኝ ወይስ በረከት ግራኝ? (ክፍል 2)
- የወርቅ ኢዩቤልዩ እንዲህ አይከበርም ያለ ማነው? የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መን...
- Ayalew Gobeze named "Ayalew Gragn"
- የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራ
- “አዘክሪ” - አዲስ ብሎግ (ግለ-ጦማር)
- Patriarch Paulos Denied Ark News
- እግድ የተጣለባቸው የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ስብሰባ አካሄዱ
- በደሴ ከተማ በምዕመናንና ፖሊስ መካከል በተደረገ ግጭት ሁለት ሰዎች ተገደሉ
-
▼
July
(75)
11 comments:
Dear Abel Zekedamawi,
Very good contribution. Especially for those of us who do not know what the role of the Holly Synod, suck contributions are really important. Till our Ethiopian Orthodox Church is free from racist, political(cadre), and corrupted mischievers like aba Gebremariam(aba Paulos the killer)and his supporters like Mahbere kidusans, we need to inform the right thing to the follower of the Church,
Ab.
Dear Abel Zekedamawi,
Very good contribution. Especially for those of us who do not know what the role of the Holly Synod, suck contributions are really important. Till our Ethiopian Orthodox Church is free from racist, political(cadre), and corrupted mischievers like aba Gebremariam(aba Paulos the killer)and his supporters like Mahbere kidusans, we need to inform the right thing to the follower of the Church,
Ab.
DS ebakachu be Abel Zekedamawi kwtawu hgebetkirstian lay yagenagnachut web tiru aydelm ena ybet kirstian heg slhon erasun chlo mwutat eyechalachu magenagnetu beni eyta selam alsetgnm ena lytachu ahununu betawtut elalehu.
medehanealm yirdan
kidane mariam k axsum.
dear anonymous #1,i think so you are confused. Mahibere Kidusan is not the supporter of Aba Paulos but Mk supported an also will support the structure of our Tewahido Church. Our church has a liable structure from the sigle church(atbiya)to the Holly Synode.The problem is we all never practically use it, that why the things is mised up now. please don't be confuse and don't connect MK and Aba paulos. if you have time please read Qale Awade(structure of our church).
Corrections to Anonymous1 and 2:
-Anonymous1:-
Aba Paulos is not Gebremariam....he is Gebremedihin.
I saw that you are mixing stuff which you don't know about.
-Anonymous2 .... yes you will not have peace until you totally dismantle the church. I know why you hate that web site. They are the once who expelled all Menafiqan from our holy church!
GOD bless Ethiopia
Folks this may help you too.
the Holy Synod of any Orthodox Church is the highest authority of the Church it is guiding to the truth. It formulates the rules and regulations of the church organization, faith and order of service. It should be chaired by the Patriarch and Bishops who all seek one goal.
God is Wonderfyl in His Saints, The God of Isreal. Please let us pray that we may complete the remaining time in peace and repentance.
"The righteous called, and the Lord hears, and delivers them out of all their troubles." psalm 34:17
በተቻለ መጠን የመንፈሳዊ ጉዳዮችን እየተወያየን ከስድብና ፣አጸያፊ አባባሎች እንጠንቀቅ።በአጠቃላይ በሲኖዶሱ ብሎም በአባ ፓውሎስ የተፈጠረው ችግር፣የወያኔ
ስርአት ውልድ ነው። ወያኔ እስከ መጨረሻው ስራአቱ ከኢትዮጵያ መሬት እስካልወደመ ድረስ ሲኖዶሱን ብቻ አስተካክላለው ማለት፣በበሺታ ከተለከፈ ዛፍ አንድ ቅጠል ብቻ በመበጠስ መላ የዛፍ ተክሉን አድናለው ብሎ እንደመሞከር ነው።
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ለብዙ ሺ ዘመናት ከኢትዮጵያ ስርአት ጋር የተያያዘ ነው።ፈሪሀ እግዚአብሔር ያላቸው መሪዎች ሲሾሙ ቤተ ክርስቲያኗ ስትጠነክር፣እንደ መለሰ ዜናዊ ያሉ ጸረ ማሪያሞች ደግሞ በስልጣን ላይ ሲቀመጡ የደረሰውን የምናየውና የምንሰማው ነው።
በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ የሃይማኖቱ ሕልውና ከኢትዮጵያ እንደ አንድ አገር ከመኖር ጋርም የተያያዘ ነው።ልብ ብለን ልንገነዘበው የሚገባ ነገር ቢኖር፣የኢትዮጵያ መበታተንና መጥፋት፣የኢትዮጵያ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ገዳማት፣የቅኔ የድጓ ትምሕርት ቤቶች መበታተን ማለት ነው።አገራችን ኢትዮጵያ ከጠፋች የሃይማኖታችን ሕልውና በትልቅ አደጋ ላይ እንደሆነ ልናስብበት ይገባል።የወያኔ ትልም አገርን ማጥፋት፣ኢትዮጵያን መበታተን እስክ ሆነ ድረስ፣ሃይማኖታችንም ሊያጠፋ እንደተዘጋጀ ጠላት ከመሆን አይዘልም።
ዛሬ የሲኖዶሱ ብክለት ከወያኔ ከጠቅላላ ክርፋት የመጣ ነው።ይሕ ሲኖዶስ ዛሬ ጸዳ ቢባል የወያኔ ስርአት አስካለ ድረስ ነገ በሌላ በሙስና በተለከፈ ሲኖዶስ እደሚተካ አያጠራጥርም።ጉልቻ ቢቀያየር ወጥ አያጣፍጥም።
በተለይ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታዮች ልናደርገው የሚገባ ነገር ቢኖር በመጀመሪያ ደረጃ ዘመቻውን በራስችን ላይ አድርገን ከባሕል ሃይማኖተኛ ከመሆን ወጥተን፣ዶግማውን ቀኖናን ተገንዝበን ትክክለኛ አማኞች ለመሆን መጣር።በሁለተኛ ደረጃ በየጥቃቅኑ ነገር ልዩነት እየፈጠርን ጊዜ ከማጥፋት፣ልዩነቶችን ከማስፋት፣አገርን ክጥፋት ለማዳን፣ጽኑ ሃይማኖታችንን ለመጥበቅ በድርጅት መንቀሳቀስ ይጥበቅብናል።
ሃይማኖትና ፖለቲካ አብረው አይሄዱም የሚል አባባል የወያኔና የካድሬዎቹ ማደነጋገሪ መሆናቸው ልብ እንበል። በኢትዮጵያ ታሪክ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶና ቤተክርስቲያን እና መነግስት የተለያዩበት ጊዜ የለም።ስርአቱ ሲጠራ ብቻ ነው ቤተክርስቲያኗ የምትጸዳው።
ወያኔ አሁን በሲኖዶሱ የተፈጠረው አይነት ሁኔታዎች
ይወዳቸዋል።ሕዝብን ከዋናው ትግል ያዘናጉለታል።ወያውን
ከስልጣን ከማውረድ የሚደረገውን ትልቅ የትግል አካል
ይሸርፈዋል።
አመልማል ክፍሌ
Tehadso was expecting that Aba Merkorious would be the next Patriarch if Aba Paulos were removed from his position. All tehadso members, please don't expect to come to the power again, as you are out of the Synod line. The existence of the so called false Synod of America is annahilated by the power of God.
Thanks a lot Amelia!
I agree with you 101%. We can't make the church alone "an island of democracy".
By now everything/every institution, be it civil, social or religious, is under the control of Weyanie. So we have no choice. Unless the country is ruled by true leaders the problem will worsen.
Weyanie likes division....by its nature. So dear Dejeselam, when you moderate the comments ... please filter out messages that have the intention of dividing the Chrstians.
Egzer yabertachihu!
Dear DEJE SELAM,
Every one is posting a message here including:
-- Tehadso
-- Protestants
-- Ismaelawuyan.....
So please don't open the door for them to attack us. Keep on moderating the messages.
Ye Kidus Michael Amalajinet Ayileyen
Post a Comment