
(ከደጀ-ሰላማዊው)
ዜና አስውቦ ማቅረብ ገንዘብህ ነበረ፣
አሁን ሐሰት ገዛህ ተከተተ ቀረ።
ቅንነት የሌለህ ለጥቅም የተጋህ፣
ለካስ ትንሽ ሰው ነህ ገንዘብ የሚገዛህ።
ወሬ ለአገር ላይጠቅም ሥልጣን ላያረጋ፣
ሰጪ እና ተቀባይ ሥራውን ዘነጋ።
ምን ነበረ ቢቀር ጉዳችሁ ባይወጣ፣
በአንድ መቶ ሺህ ብር የሚሊዮን ጣጣ።
አተርፋለሁ ብለህ ንጉሤ ተሞኘህ፣
ላትገፋው ጀምረህ ግብርህ አጋለጠህ።
ለእናት ኢትዮጵያ ተቆርቋሪ መስለህ፣
ዜና ስታሰማ ጉቦ በሉ ብለህ፣
ብዙ ጊዜ ሰማን የአንተ አድማጮች ሆነን፣
ዛሬ ተረኛ ነህ አንተ ደግሞ አድምጠን።
ይኼ ነው ንጉሤ አሰማኸን ብሥራት፣
አንተው ጉቦ በላህ የዜናው ባላባት።
ምን ዓይነት ሎተሪ ምን ዕጣ ገጠመህ?
“አባ ይፍቱኝ” ልትል ልትሳለም ሄደህ፣
መፍታቱን ተዉና እነሆ ጉድ ሠሩህ፣
በአንድ መቶ ሺህ ብር የፊጥኝ አሰሩህ።
ያለ ግብሬ ልግባ እንዲህ ከሆናችሁ፣
ሰጪና ተቀባይ እግዚአብሔር ይፍታችሁ።
የሰየምከው ጣቢያ “ሀገር ፍቅር” ብለህ፣
“ፀረ ሀገር” ተብሏል በቃ አድማጭም የለህ።
ሁለት ሞት አትሙት በጉቦ እና በሐሰት፣
ብሩን መልስና ተመለስ ወደ እውነት።
((ደጀ ሰላም፤ ጁላይ 21/2009: ይህ ግጥም የተጻፈው ለሀገር ፍቅር ሬዲዮ አዘጋጅ፣ $10000 ዶላር ተቀብሎ አባቶችን በማንጓጠጡ በተቀየሙ አንድ ምእመን ነው።)
5 comments:
thank you .
keep up it is very good talent.
how ever wrote God Bless you.
KOMATAN KOMATA KALALUT GEBETO YEFETEFTAL .
Bravo Bravo! tell him to this Werobela
He is being rejected he is now Telala!
ኑጉሤ እረ አንተስ የተዋሕዶ ጠላት....አንተንስ የእግዚአብሔር እጅ ይክበድሕ። የሚቀጥለው መልክቴ ደግሞ New York ለሚገኝት አባት(ጳጳስ) የፀሎት ሠው ከሆኑ ወደ ቅድስት ሐገሮት ኢትዬጵያ.እረ እንደው የጠፉውን ገንዘብ ምዕመኑን ጠይቄ እከፉላለው ሲሉ ቅር አይሎትም።ለተቀሩት ደግሞ ምንም አናቅም ላላችሁት አፈርናባችሁ፤በመጨረሻም ለደጀሠላም አዘጋጅ የቤተክርስቲያን ገንዘብ ያጠፉ ካኽን,ምን ይላል?
ayee Niguse,now u r not called Niguse but Yihuda,10,000 dollar endenekesk endatimot niseaha giba.alya ende yihuda-yihuda weldu welewiludu yidemises,sibal eskezelalem sitiregem tinoraleh,maferyaaaaaaa
anten blo niguse any ways i know u u know me bekirb ken kegonh tagegaleh if u wnt where DC leza yabkan ante yehager and cherech telat
Post a Comment