(ደጀ ሰላም፤ ጁላይ 8/2009)
ያለ ፓትርያርኩ ፍላጎትና ፈቃድ፣ ፓትርያርኩን ያልጨመረው የመጀመሪያው የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ በማካሄድ ላይ ይገኛል። ስብሰባው ዛሬ ረቡዕ ጠዋት ሲጀመር ጉባዔውን ለማቋረጥ ብዙ ሙከራ ያደረጉት ቅዱስነታቸው ሳይሳካላቸው ቀርቷል ተብሏል። በመጨረሻም አጀንዳው ቀርቦ ሊጸድቅ ችሏል። የዕለቱ ብቸኛ አጀንዳ “በቅዱስ ፓትርያርኩ የተፈጸሙ አስተዳደራዊ በደሎች” በመሆናቸው ይህንን አጀንዳ ለመመልከት በሕገ ቤተ ክርስቲያን መሠረት ቅዱስነታቸው መውጣት እንዳለባቸው ሲነገራቸው አሻፈረኝ ብለዋል። በዚህ መልኩ ለብዙ ሰዓታት ብጥብጡ ቀጥሎ በመጨረሻ ቅ/ሲኖዶሱ ሁሉጊዜም ከሚካሄድበት አዳራሽ በመውጣት አባቶች ባገኙት በሌላ ሥፍራ በመካሄድ ላይ ይገኛል።
ጉባዔው ስብሰባውን ሲቀጥል ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ በሰብሳቢነት እንዲመሩ የመረጣቸው መሆኑም ታውቋል።
ይህንን ጉባዔ ለማካሄድ ብዙ እንቅፋት ገጥሞት እንደነበር የደጀ ሰላም ምንጮች አስታውቀዋል። በተለይም የቅዱስነታቸው ደጋፊዎች የሆኑት ብፁዓን አበው ገብርኤል፣ ይስሐቅ፣ ገሪማ፣ ኤርምያስና ሙሴ አደናቃፊ ተግባራትን ሲፈጽሙና ሲያስፈጽሙ ነበር ተብሏል። በተጨማሪም ብፁዓን አባቶችን በስልክ “እንገላችሁዋለን፣ እናጠፋችሁዋለን” እያለ የሚያስፈራራው የወ/ሮ እጅጋየሁና የግብረ አበሮቻቸው ቡድን በዚሁ ተግባሩ ቀጥሏል ተብሏል። ሴትዬዋ ሽጉጥ መታጠቃቸውን ቢያንስ በሁለት አጋጣሚዎች ያሳዩ ሲሆን በሙስናና በቤተ ክርስቲያን ዝርፊያ ሀብታም የሆኑት ሰዎች ቡድን በብፁዓን አባቶች ላይ አደጋ እንዳይጥል መንግሥት ጥበቃ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ ጉዳዩን በጥሞና በመከታተል ላይ የሚገኘው መንግሥት “የቅዱስ ሲኖዶስን ውሳኔ እንደሚቀበል” ፍንጭ ማሳየቱ ታውቋል። ነገሩ በርግጥ በዚህ መልክ ከቀጠለ እና መንግሥት የቤተ ክርስቲያን አባቶችን ውሳኔ አክብሮ ከተቀበለ በማስፈራራትና “ወየውላችሁ መንግሥት ከኔ ጋር ነው” የሚለው ቅዱስነታቸው ዛቻ ፍሬ ያጣል ተብሎ ይጠበቃል። ይህም ቤተ ክርስቲያን በርግጥም ራሷን በራሷ በእውነተኛ ነጻነት ማስተዳደር የምትጀምርበት አዲስ ምዕራፍ እንዲከፈት ያደርገዋል።
ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን!!!!!!!!
ቸር ወሬ ያሰማን
አሜን
July 8, 2009
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
Blog Archive
-
▼
2009
(275)
-
▼
July
(75)
- ጠቅላይ ቤተ ክህነት “አዲስ ነገር ጋዜጣን” ከሰሰ
- +++++++ - - - - - - ???? ?? About Mahibere Kidusa...
- "ኘትርክናው ከሆነላችሁ መልካም" ግብጻውያን
- ለቅዱስነትዎ ይድረስ
- ‘‘ለሀገር ፍቅር ሬዲዮ" አዘጋጅ ለአቶ ንጉሤ የተሰጠ መጠነኛ አስተያየት
- በደብረ ሰላም መድኃኔዓለም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ሚኒያፖ...
- ርዕሰ አንቀጽ፦ “ደጀ ሰላም” የማን ናት?
- እስከ ጥቅምት ቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ ምን እንሥራ?
- አቡነ ቄርሎስ የቤተ ክህነት ግቢን ለቀቁ
- ፓትርያርኩ የአዲስ አበባ ገዳማትና አድባራት ኃላፊዎችን ሰበሰቡ፤ መመሪያ ሰጡ
- ጉዞ ወደ እስክንድርያ በድጋሚ? እንዴት ተደርጎ!!!
- ‹‹ማርቆስ አባታችን እስክንድርያ እናታችን›› ብለን ወደ ቀደመው ድንኳን እንሂድ...
- ድንቄም ተቆርቋሪ
- የወቅቱን የቤተ ክርስቲያን ችግር አስመልክቶ ብፁዕ አቡነ አብርሃም ጥሪ አስተላለ...
- የቤተ ክህነቱ ማፊያ ቡድን አሁንም አልተያዘም፤ ውንብድናው ከተፈፀመ ሳምንት ሆ...
- “ብሩን መልስና ተመለስ ወደ እውነት” (ለንጉሴ ወ/ማርያም)
- የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ዝግጅት በቅንጭቡ፤ ኪነ ጥበባዊ ቅንብር በዳን
- ጳጳስ
- የማፊያው ቡድን ድምጽ ንጉሴ ወ/ማርያም ፓትርያርኩ “ገንዘብ በመቀበል ጵጵስና ይ...
- የሎንዶን ደ/ሰ/ቅ/ማርያም ሰበካ ጉባዔ በአባቶች ላይ የተፈጸመውን ወንጀል አወገ...
- ሰበር ዜና (Breaking News) መንግሥት “ፓትርያርኩን ተቃወሙ” ያላቸውን ...
- “ፓትርያርኩ አሸነፉ” መባሉን አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች ተቃወሙ፤ ሌሎች ደገፉ...
- የማፊያው ቡድን ድምጽ በአሜሪካ “ማጥቃት” ጀመረ፤ የቁልቢ ብር ሥራውን እየሠራ ...
- አንዳንድ ነጥቦች ስለ ሕገ ቤተ ክርስቲያን
- ስለ ቅ/ሲኖዶስ ስብሰባዎችና ውሳኔዎች ሒደት የአዲስ ነገር ጋዜጣ ልዩ ሪፖርታዥ
- Comments To Be Moderated
- የግርግሩ ፍጻሜ ማግሥት
- የሁለቱ ወር የቅ/ሲኖዶስ ውጣ ውረድ ሲጠቃለል፤ ሪፖርታዥ
- ስውሩ የአቡነ ጳውሎስ እጅ ድል አደረገ፤ ስብሰባው “የፓትርያርኩን አቋም በመደገ...
- People Who Attacked Ethiopian Bishops Are not Arre...
- የቤተ ክህነቱ ማፊያ ቡድን አሁንም አልተያዘም፤ የመንግሥት ደህንነቶች ሳይኖሩበት...
- አባቶች አካላዊ ጉዳት እንዳልደረሰባቸው ታወቀ
- (ሰበር ዜና፣ Breaking News) ብፁዓን አባቶች ላይ አደጋ ተጣለ
- የሥራ አስፈጻሚው ዕገዳ ተነሣ
- በመንግሥት አደራዳሪነት ዝግ ስብሰባ እየተደረገ እንደነበረ ታወቀ
- ሪፖርተር ጋዜጣ የተሳሳተ መረጃ እያሰራጨ ነው
- Question And Answers About the Holy Synod Meeting:...
- Challenge the Idea Not The Person: How Deje Selam ...
- ሰበር ዜና (Breaking News):- አባቶች በመጨረሻ ተፈራረሙ!!!! የፈረሙ...
- ለአጋእዝተ ዓለም ቅድስት ሥላሴ በዓል እንኳን አደረሳችሁ
- የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ ዛሬ ማክሰኞም ይቀጥላል
- አቡነ ገብርኤልና አቡነ ሙሴ ለምን ያውካሉ?
- ይህ ሁሉ ስለምን ደረሰብን? ምንስ እናድርግ?
- ስብሰባው ያለምንም ውሳኔ ተበተነ
- ቅዱስ ሲኖዶስ በፓትርያርኩ ሰብሳቢነት እየተነጋገረ ነው
- የጥብዐት ቁልፍ - Key To Resolution
- የብፁዕ ወቅዱስ ሥልጣን “ልጓም እንዲበጅለት” የሚፈልጉ ወገኖች እነማን ናቸው?
- “ቸር ወሬ ያሰማን”
- ግብር አልባ ለሆነው የሥልጣን ወንበር ጥበቃ የተደረገ ሞት ሽረት
- መንግሥት አቋሙን ገለጸ፣ አቡነ ሳሙኤል ተለቀቁ፣ ስብሰባው ይቀጥላል
- በተዋሕዶ ነን ወይ ?
- ምርጥ ንግግሮች ስለ ወቅቱ የቤተ ክርስቲያናችን ጉዳይ
- እግዚአብሔርን ተስፋ አድርግ፤ በርታ፥ ልብህም ይጽና፤
- ሰበር ዜና (Breaking News) እና ሪፖርታዥ፦ የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ በአ...
- ወ/ሮ እጅጋየሁ ወይስ የዘመኗ ኤልዛቤል?
- ቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔው ላይ ሳይፈርም ቀረ፤ ጋዜጠኛው ተደበደበ
- ቅ/ሲኖዶስ የፓትርያርኩን “ሁሉን አቀፍ ሥልጣን” ገፈፈ፣ “እንደራሴ” ሾመ
- ደጅሽ ላይ ቆሜ እጠራሻለሁ
- በሃይማኖት ጣልቃ አለመግባት እስከ ምን?
- የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ ቀጥሏል
- “ማኔ ቴቄል ፋሬስ” (ትንቢተ ዳንኤል ምዕራፍ 5) “እግዚአብሔርን የማያውቁ የእ...
- ቅ/ሲኖዶስ ዛሬም ሳይሰበሰብ ቀረ
- “የቅዱስ ሲኖዶስ ስብሰባ ያለ ፓትርያርኩ መሪነትም ቢሆን ይካሄዳል” (ቋሚ ሲኖዶ...
- "ለቅዱስ ሲኖዶስ ውሳኔ ተግባራዊነት የሚጠበቅብንን ሁሉ በማድረግ እንትጋ"
- በዘመናት መካከል የተገኘ ዘመን የማይሽረው ልዕልና
- አስቸኳዩ የቅ/ሲኖዶስ ስብሰባ እንዳይካሄድ ከፓትርያርኩ ተቃውሞ ቀረበ
- ግልጽ ደብዳቤ ለብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ በእስዎም በኩል ለቤተ ክርስቲያኗ ሲ...
- አያሌው ግራኝ ወይስ በረከት ግራኝ? (ክፍል 2)
- የወርቅ ኢዩቤልዩ እንዲህ አይከበርም ያለ ማነው? የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን መን...
- Ayalew Gobeze named "Ayalew Gragn"
- የቅዱስ ሲኖዶስ አስቸኳይ ስብሰባ ተጠራ
- “አዘክሪ” - አዲስ ብሎግ (ግለ-ጦማር)
- Patriarch Paulos Denied Ark News
- እግድ የተጣለባቸው የፓትርያርኩ ረዳት ሊቀ ጳጳስ ስብሰባ አካሄዱ
- በደሴ ከተማ በምዕመናንና ፖሊስ መካከል በተደረገ ግጭት ሁለት ሰዎች ተገደሉ
-
▼
July
(75)
7 comments:
Egzihabeher Yefekedewn Ersu Yemkeberebeten Be kiduse Sinodose Yesera. Amen!
YeAbatachin YeTsadiqu Abune Tekle Haimanot Amlak Yirdan! Bezih Kiffu Weqt Tewahedo Haimanotachinin'ina Hizbe Kristianun YiTTebiqilin. Seif
Kemezezubin YeDiabilos Meleiktegnoch YeTTifat Mikirina BeDem YeTTaTTebe Ejachew Yadinen
KeMiTTadu Wede Welafenu Endaihon Beyalenibet BeQoraTTinet'ina Kristianawi Qinie'at YeDirshachinin EniweTTa.
YeDessie Quidist Arseman Miemenan'ina BeMela Agerachin BeDem Yekefelnewin Meswaetinet Belibachin Yizen Enaleqsalen.
Egzio Meharene Kristos!
BeEnte EgziEtine Mariam Meharene Kristos! Amen.
መጽሐፈ ነህምያ 9- 32
አሁንም አምላካችን ሆይ፥ ቃል ኪዳንንና ምሕረትን የምትጠብቅ ታላቅና ኃያል የተፈራኸውም አምላክ ሆይ፥ ከአሦር ነገሥታት ዘመን ጀምሮ እስከ ዛሬ ድረስ በእኛና በነገሥታቶቻችን በአለቆቻችንም በካህናቶቻችንም በነቢያቶቻችንም በአባቶቻችንም በሕዝብህ ሁሉ ላይ የደረሰው መከራ ሁሉ በፊትህ ጥቂት መስሎ አይታይህ።
በደረሰብንም ነገር ሁሉ አንተ ጻድቅ ነህ፥ አንተ እውነት አድርገሃልና፥ እኛም ኃጢአት አድርገናል። ነገሥታቶቻችንም አለቆቻችንም ካህናቶቻችንም አባቶቻችንም ሕግህን አልጠበቁም፥ የመሰከርህባቸውንም ትእዛዝህንና ምስክርህን አልሰሙህም።
በመንግሥታቸውም በሰጠሃቸውም ታላቅ በጎነትህ፥ በፊታቸውም በሰጠኸው በሰባው ምድር አላመለኩህም፥ ከክፉም ሥራቸው አልተመለሱም። እነሆ፥ ዛሬ ባሪያዎች ነን፤ ፍሬዋንና በረከትዋን ይበሉ ዘንድ ለአባቶቻችን በሰጠሃት ምድር፥ እነሆ፥ በእርስዋ ባሪያዎች ነን፥ ስለ ኃጢአታችንም ለሾምህብን ነገሥታት በረከትዋን ታበዛለች፤ ሰውነታችንንም ይገዛሉ፥ በእንስሶቻችንም የሚወድዱትን ያደርጋሉ፥ እኛም በጽኑ መከራ ላይ ነን።
maren yekere belene,beza hunen
Zebe'entiAha leBeteKristian tetsefa'eke bewesete awede kemeteqedesa bedemeke kebure
ጸልዩ በእንተ ሰላመ ቤተ ክርስቲያን
ሁላችን በያለንበት፡ የሦስቱን ለጆች ጸሎት እየጸለይን፡ እግዚአብሔርን ደጅ እንጥና፡፡ በሓዋርያት ጾም ማለቂያ፡ ሊያሰማን ያሰበው ይኖር ይሆናል፡፡
በጸሎት እንበርታ!
I am glad that we have reached this stage where transparency and accountability is being practiced (though it is at its infant stage). This is how the leadereship works. Let God help our church and our country.
Please, keep on updating us the church related issues and let us know what we have to do to improve the church services accross the country and in the diaspora.
God Bless you
መለስ ዜናዊ ሌላ ጳጳስ ሊቀይርልን አስብዋል። ይህ ምኑ ነው የሚያስፈነድቅ? ወያኔ ሳይፈልግ የሚሰራ አንዳችም ነገር የለም። ፓትሪያሪኩ ህዝብ አልቀበል ስላላቸው ሌላ የተዘጋጀልን አለ ማለት ነው። መንግሰት ጣልቃ አይገባም ነው ያሉት ጸሃፊው? ማነው ሰሞኑን ጣልቃ ገብቶ ወሎ ላይ ምእመናኑን እየፈጀ እያስፈጀ ያለው? እባካችው የመለስ ዜናዊ እቃ እቃ ጨዋታ ይግባችው።
የቀራኒዮ በግ ስለ ኢ.ኦ.ተ ልጆች ለተኩላ ስለ በተናችሁ ደሙን ከእጃችዉ ይፈልጋል.
“ማኔ ቴቄል ፋሬስ” በመዳፍ እጃችሁ ይጽፋል.
Post a Comment