January 26, 2012

ጥምቀት በለንደን


(ተዋሕዶ ዘሎንዶን፤ ለደጀ ሰላም፣ ጥር 17/2004 ዓ.ም፤ January 26/2012/ READ THIS ARTICLE IN PDF)፦ የ፳፻፬ ዓ.ም. የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ጥምቀት በዩናይትድ ኪንግደም ርዕሰ ከተማ ለንደን በከፍተኛ መንፈሳዊ ስነ-ሥርዓት መከበሩን የሰ/ምዕ/አውሮፓ /ስብከት /ቤት አስታወቀ። ጌታ ወደ ዮርዳኖስ ወንዝ ወርዶ መጠመቁን ለማዘከር በቆየው የቤተ ክርስቲያን ሥርዓትና ትውፊት መሠረት በለንደን የሚገኙት የኢ///አብያተ ክርስቲያናት በበዓሉ ዋዜማ ታቦቶቻቸውን ይዘው ከመቅደሶቻቸው ሲወጡና ለማደሪያ በተዘጋጀላቸው ሥፍራ ሲደርሱ ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን፣ ካህናት፣ የሰንበት /ቤቶች ወጣት መዘምራን በያሬዳዊ ዜማና ዝማሬ፤ ምዕመናን በእልልታና ደማቅ የአምልኮት ስነ-ሥርዓት አሸኛኘትና አቀባበል አድርገውላቸዋል።

January 24, 2012

የዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ የአደባባይነት ቅርስነቱ አበቃ?

  • አቡነ ጳውሎስ በተገኙበት በዐፄ ዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ የነፈሰው ማዕበል መሰል ውቅንብል ነፋስ የባሕረ ጥምቀቱን ሥነ ሥርዐት ለሩብ ሰዓት አስተጓጐለ::
  • ማዕበል መሰሉ ነፋስ “መልአከ እግዚአብሔር ወርዶ እየባረከ ነው” የሚል ትርጉም ቢሰጠውም በምእመኑ ዘንድ ግን የአስከፊ ድርጊት ንግር ተደርጎ ተወስዷል::
  • የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ ላይ አገልግሎት ሰጪ ሕንፃ ሊያስገነባ ነው፤ ታሪካዊው አደባባይ የደብረ ብርሃን ከተማ አብያተ ክርስቲያን ባሕረ ጥምቀት እና መስቀል ደመራ የሚያከብሩበት ነው::
(ደጀ ሰላም፣ ጥር 15/2004 ዓ.ም፤ January 24/2012/ READ THIS ARTICLE IN PDF)፦ ምድር መሠረት፣ የሰማይ ዐምድ የሆነው ረቂቁ ነፋስ በእግዚአብሔር ትእዛዝ እንደሚነሣ፣ እንደ ዐውሎ (ጥቅል) ሆኖ ሲነፍስም ድንገቴ ነውና የእግዚአብሔር ፍርድ ምሳሌ እንደሆነ ይታመናል (መዝ.106(107)÷25፤ ምሳ. 10÷25፤ ኢሳ. 17÷13፤ ናሆም 1÷3)፡፡ ጥር 13 ቀን 2004 ዓ.ም በደብረ ብርሃን ከተማ በታሪካዊው ዘርዐ ያዕቆብ አደባባይ እና አካባቢው የታየው ይህንኑ የሚያጠይቅ ነው ተብሏል፡፡

Addthis Sharing Gadget

Blog Archive