April 26, 2013

የስብከተ ወንጌል ቀን በእለተ ሆሳዕና


       (READ IN PDF)
v በውኑ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ወንጌል አትሰብክምን ?
 v በቅድስት ቤተክርስቲያን ያለው የስብከተ ወንጌል አገልግሎት ምን ይመስላል ?
 v በማስተማር : በሕትመት : በድረ ገጽ : በራዲዮና ቴሌቭዥን ....
 v ማኅበረ ቅዱሳን በስብከተ ወንጌል አገልግሎት ዙሪያ ምን እያደረገ ነው?
 v ስለ አሥሩ ዓመት የስብከተ ወንጌል መርሐግብር (2011 ፕሮጀክት) ያውቃሉ ?
 v ስብከተ ወንጌልን በጋራ እንዴት እናስፋፋ ? የእኛ ድርሻ ምንድን ነው?
 v በሀገር ቤት :  በውጭው ዓለም/ በዳያስፖራ

April 18, 2013

ደጀ ሰላማውያን ሁሉ፣ እነሆ ተመልሰናል


(ደጀ ሰላም፤ ሚያዚያ 10/2005 ዓ.ም፤ ኤፕሪል 18/2013/ READ IN PDF)እንደምን ሰነበታችሁ፣ እንደምን ከረማችሁ። ልክ በወራችን ብቅ አልን። በዚህ አንድ ወር ውስጥ እጅግ በጣም ብዙ ክስተቶች እንደተስናገዱ እናውቃለን። ከዐቢይ ጾም ጅማሬ እስከ ቅድስት ሥላሴ ኮሌጅ ተማሪዎች ትምህርት ማቆም፣ የረሃብ አድማ እና ችግር ድረስ። ሁሉንም በየፈርጁ እንደ አቅማችን ወደፊት የምንተነትነው ሆኖ ለዛሬ ግን በነቢዩ አልያስ ስም ዙሪያ እና “ድጋሚ ወደ ምድር መምጣት” ስም በተጀመረውና የሰሞኑ መወያያ በሆነው ጉዳይ እንጀምር። ማኅበረ ቅዱሳን ጠቅለል ያለና ለሁሉም ዓይን ገላጭ የሆነ ጽሑፍ “ተረፈ አይሁዳዊነት በኤልያሳዊነት ስም ሲበቅል” የሚል ጽሑፍ አቅርቧል። የሚችል በጥልቀት፣ ጊዜ የሌለው ደግሞ በወፍ በረርም ቢሆን ነጥቦች ይያዛቸው። ለውይይት መነሻ ይሆናል።

March 19, 2013

"30 000 ኢትዮጵያውያንን ለጨፈጨፈው ለግራዚያኒ የተሠራውን ኃውልት መቃወም ያስከብራል!" (ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ)


                                               www.globalallianceforethiopia.org
        ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ - የኢትዮጵያ ጉዳይ
                  4002 Blacksmith Drive, Garland, TX 75044, USA
                              መጋቢት 9 ቀን 2005 ዓ/ም
መግለጫ (PDF)
30 000 ኢትዮጵያውያንን ለጨፈጨፈው ለግራዚያኒ የተሠራውን ኃውልት መቃወም ያስከብራል!
በኢጣልያ፤ ከሮማ ወደ ምሥራቅ ደቡብ በምትገኝ፤ አፊሌ በምትሰኝ ትንሽ ከተማ፤ “የኢትዮጵያ ጨፍጫፊ” ለተሰኘው፤ ለሮዶልፎ ግራዚያኒ ነሐሴ 4 ቀን 2004 ዓ/ም የቫቲካን ተወካይ በተገኙበት የተመረቀለትን የክብር መታሰቢያና መናፈሻ በመቃወም፤ እስከ የኢጣልያ ኤምባሲ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ለማከናወን መጋቢት 8 ቀን 2005 ዓ/ም ስድስት ኪሎ የተሰበሰቡትን 43 ሰዎች፤ ዶር. ያዕቆብ ኃይለማርያምን ጭምር፤ ፖሊስ አፍሶ ማሰሩና በማግስቱ፤ መጋቢት 9 ቀን 2005 ዓ/ም መልቀቁ ታውቋል።

March 5, 2013

በውጪ አገር ያሉትን አባቶች ያጋልጣል የተባለ ትንሽ መጽሐፍ ተሰራጨ


  • ቤተ ክህነቱ ይህንን ያደረገው ዕርቁ የፈረሰው በውጪዎቹ ችግር መሆኑን ለማጠየቅ ነው፤
  • የደጀ ሰላም ምንጮች “ቤተ ክህነታዊ ሐረካት” ብለውታል። 

(ደጀ ሰላም፤ የካቲት 26/2005 ዓ.ም፤ ማርች 5/2013/ PDF)በስደት የሚገኙነትን አራተኛው ፓትርያርክ ጨምሮ በውጪ አገር ያሉ አባቶችን ስሕተት፣ ጥፋትና ዕርቀ ሰላሙን ማፍረስ የሚያትት እንዲሁም ፓትርያርኩ ከሥልጣን የወረዱት ተገደው ሳይሆን በራሳቸው ፈቃድ መሆኑን የሚያትት ባለ 52 ገጽ አነስተኛ መጽሐፍ ታትሞ በመሰራጨት ላይ ነው።

ከ5ኛው ፓትርያርክ ግድፈቶች መካከል አሁንም እንዳይደገሙ መታሰብ ያለባቸው ነጥቦች

(ደጀ ሰላም፤ የካቲት 26/2005 ዓ.ም፤ ማርች 5/2013/ PDF)ይህ ጽሑፍ “ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ፣ ወእጬጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱምና የዓለም አብያተ ክርስቲያናት ለሰላም የክብር ፕሬዚደንት፣ በቅድስት ቤተ ክርስቲያን ላይ የፈጸሟቸው ዐበይት ችግሮች፤ የኢትዮጵያ ኦርቶዶከስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ዋና ዋና አንገብጋቢ ችግሮች እና መፍትሔዎች፦ ከፍተኛ ትኩረት የሚሻ” (ግንቦት 2001 ዓ.ም፤ ከገጽ 3-9) በሚል ርዕስ ከዚህ በፊት (August 5/2009) ያቀረብነውን ለተሾሙት አዲስ ፓትርያርክ ተሞክሮ ይሆኑ ዘንድ ያቀናበርነው ነው።

Blog Archive

ነጻ ፓትርያርክ ምርጫ ቢሆን ኖሮ ማንን ይመርጡ ነበር? እንበልና ሁሉም ነገር ሥርዓቱን ጠብቆ የተከናወነ የእጩዎች ምርጫ ቢሆን ኖሮ፣ አሁን የምናነሣቸው ጉድለቶች ባይኖሩ ኖሮ፣ 6ኛው ፓትርያርክ እንዲሆን የምትመርጡት ማንን ነበር? (ማሳሰቢያ፦ አሁን ያለው ክፍፍል እና የመንግሥት ተጽዕኖ ባይኖር ኖሮ ተብሎ የሚመለስ ጥያቄ ነው። የምን “ባይኖር ኖሮ ነው” የሚል አስተያየት ካለዎትም እናከብራለን።)